Wednesday 29 April 2015

the scandalous details surrounding the Clinton Foundation highlighted in the soon to be

ወይ ይች ሀገር!!
ሼህ መሀመድ ሁሴን አል አሙዲን ለክሊንተን ፋውንዴሽን በ2006 ዓመተ ምህረት 20 ሚሊዮን ዶላር መስጠታቸውን ፒተር ስዋይዘር የተባሉ ጸሀፊ በቅርቡ ለህተመት በሚያበቁት መጽሀፋቸው ላይ በይፋ አጋልጠዋል። (እንኳን 20 ለምን 200 ሚሊዮን ዶላር አይሰጣቸውም? ብለን ዝም እንዳንል፤ ስጦታው የተሰጠው በኢትዮጵያ መንግስት ስም መሆኑ ያማል።ይህንንም አል አሙዲ -ለፋውንዴሽኑ በጻፉት ደብዳቤ አረጋግጠዋል። ለምን በኢትዮጵያ መንግስት ስም ሰጡ? የስጦታው ምክንያት ምንድነው?የሚል ጥያቄ ከተነሳ፤ አል አሙዲ በዚያው በስጦታ ደብዳቤያቸው ላይ ፦የቡሽ አስተዳደር የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ-በክሊንተን ጊዜም ሳይቀየር እንዲቀጥል መማጸናቸው(መጠየቃቸው)ተመልክቷል።
ያንንም ተከትሎ በባለቤታቸው ስም ገንዘቡን የተቀበሉት የወቅቱ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ሄላሪ ክሊንተን የአሜሪካ መንግስት በኢህአዴግ ላይ ማእቀብ እንዲጣል ያረቀቀው አዋጅ እንዲሰረዝ ፣ ይልቁንም አሜሪካ ለኢህአዴግ አስፈላጊውን እርዳታ እንድትሰጥ ማስደረጋቸውን ደራሲው አጋልጠዋል።
(እየተዛቀ የሚወጣው የሻኪሶ (የሀገሬ)ወርቅ፤ ሀገሬን ለማፈን እንደሚውል መስማት እንዴት ያማል!!!)
“ኢህአዴግ እንድሆን ያጠመቀኝ አሰፋ ማሞ ነው” አል-አሙዲ
ለማንኛውም ይህ የአል አሙዲን እና የክሊንተን ጉዳይ በፎክስ ኒውስ ሰፊ ሽፋን ያገኘ ወቅታዊ አጀንዳ ሆኗል። ሊንኩ ከታች አለ፤ ያዳምጡት፦ አረዳው ፎክስ ኒውስ ትልቅ አጀንዳ ነው የሰጠህ። ለጊዜው እገሊትና እገሌን ተዋቸውና ይህን ጉዳይ ተወያይበት፣ተነጋገርበት..ከዚህ (ከሀገር)የሚበልጥ አጀንዳ የለም።

 http://www.realclearpolitics.com/…/fox_news_special_the_tan…

No comments:

Post a Comment