Saturday 31 December 2016

በውጭ ብድር የተጀመሩ የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታቸው ሳይጠናቀቅ የብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ


ኢትዮጵያን ስኳር ላኪ ሃገር ያደርጋሉ ተብለው ከውጭ በተገኘ ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ግንባታቸው ከሰባት አመት በፊት የተጀመሩ ፋብሪካዎች ግንባታቸው ተስተጓጉሎ እያለ ብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ።

በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ውስጥ የሚገኘው መንግስት በበኩሉ በመገንባት ላይ ያሉትን ጨምሮ በስራ ላይ ያሉ የስኳር ፋብሪካዎች ከውጭ ባለሃብቶች ጋር በሽርክና ለመስራው መወሰኑን ይፋ አድርጓል።

መንግስት ከተለያዩ አበዳሪ የፋይናንስ ተቋማት በብድር ባገኘው ገንዘብ የወልቃይት፣ የኦሞ፣ ኩራዝ አንድ ሁለትና ሶስት እንዲሁም የጣና በለስ ቁጥር አንድና ሁለት ፕሮጄክቶችን ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወሳል።

ይሁንና ሃገሪቱን ከስኳር እጥረት በማላቀቅ ኢትዮጵያ ምርቷን ወደ ውጭ ሃገር በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እንድታገኝ ያደርጋሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸው ፋብሪካዎች አብዛኞቹ በጅምር ላይ መቅረታቸው ተመልክቷል።

ፋብሪካዎቹ በከፍተኛ የፋይናንስ እጥረት ውስጥ በመግባታቸውና የተጀመሩ ፕሮጄክቶችን ለማስጨርስ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ በማስፈለጉ ምክንያት መንግስት ነባሮቹንና አዳዲስ ግንባታዎች በሽርክና ለማካሄድ መወሰኑን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ፋብሪካዎቹ በአምስት አመት ውስጥ ወደ ምርት ይገባሉ ተብሎ የተጠበቁ ሲሆን፣ ግንባታቸው በ25 በመቶ ላይ የሚገኝ እንዳለም የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን መረጃ ያመለክታል።

ፋብሪካዎች ለሰባት አመት ያህል መጠናቀቅ ባለመቻላቸው ከአበዳሪ ካላት የተገኘ ብድር የመጀመሪያ ክፍያ የመጀመሪያ ጊዜው መቃረቡን ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል።

የኮንትራት አስተዳደርና የፋይናንስ ችግሮች ፋብሪካዎቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዳይጠናቀቁ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል ዋነኞቹ መሆናቸውን የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ሃላፊ የሆኑት አቶ ጋሻው አይችሉህም ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል።

በሃሙስ ዘገባችን ለጣና በለስ የስኳር ፋብሪካ ተዘጋጅቶ የነበረ የሸንኮራ አገዳ ምርት ፋብሪካው ባለመጠናቀቁ ምክንያት ምርቱ እንዲቃጠል መደረጉን መዘገባችን ይታወሳል።

ከፋብሪካው በፊት ለምርት ደርሶ የነበረው የሸንኮራ አገዳ እንዲወገድ የተወሰነው ምርት ከፍተኛ ገንዘብ የፈሰሰበት እንደነበር ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት ይገልጻሉ።

በሃገሪቱ ያሉ ጅምርና ነባር የስኳር ፋብሪካዎችን ከውጭ ባለሃብቶች ጋር በሽርክና ለማስተዳደር የቻይንና የአውሮፓ ሃገራት በመደራደር ላይ ሲሆን፣ መንግስት ያጋጠመው የፋይናንስ እጥረት ወደዚህ አማራጭ እንዲገባ ማስገደዱንም ባለሙያዎች አስተድተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የጣና በለስ አንድና ሁለት የስኳር ፕሮጄክቶችን ለአንድ የቱርክ ኩባንያ 75 በመቶ ድርሻን ለመስጠት ሲካሄድ የነበረ ድርድር መቋረጡም ታውቋል።

በዲሳ ግሩፕ የተሰኘ ይኸው የቱርክ ኩባንያ ወደ አንድ ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ገንዘብ በመመደብ የፕሮጄክቱን 75 በመቶ ባለቤትነት ለመረከብ ድርድር ጀምሮ የነበረ ሲሆን፣ ከገንዘብ አከፋፈልና ከትርፉ ክፍፍል ጋር ከመንግስት ጋር ሊደርስ አለመቻሉ ተገልጿል።

ይሁንና ሁለቱም ወገኖች ተፈጥሯል በተባለው አለመግባባት ዙሪያ ዝርዝር መረጃን ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ኢሳት

Tuesday 22 November 2016

አንድ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በትግራይ ተወላጅ ተማሪ ዘግናኝ ጥቃት ተፈፀመበት

አንድ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በትግራይ ተወላጅ ተማሪ ዘግናኝ ጥቃት ተፈፀመበት።
በተመሳሳይ ህዳር 21 ያልተጠበቀ ጥቃት ሊፈፅሙ መዘጋጀታቸውን በቅርብ የሚከታተሏቸው ተማሪዎች መረጃውን አውጥተውታል።
የትግራይ ተውላጅ ተማሪዎች ሌሎች ተማሪዎችን መተንኮል ጀምረዋል።በተለይ በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ ተደጋጋሚ ትንኮሳዎችን አድርገዋል። ከነዚህም መካከል አክሊሉ መንገሻ የተባለ የ3ኛ አመት ማኔጅመት ተማሪ ትናንት ምሽት ጆሮውን_ቆርጠውታል፤ ልጁም ለህክምና ወደ አዲስ አበባ ተልኳል፤ወንጀል ፈፃሚውም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል ተብላል።
ቆራጩ ትግሬ ሲሆን አክሊሉ ግን የአቦምሳ (ናዝሬት አካባቢ) ልጅነው ፡፡ ልጁ ለህክምና  ወደ አዲስ አበባትናንት የተላከ ሲሆን የኢትዮ ስታር ሆቴል ባለቤት(ትግሬ )  ለማደራደር በሽምግልና ቢመጡም አልተሳካም።ሌላ ደግሞ የአደት ልጅ 3ኛ አመት ማርኬትንግ ተማሪም እንድሁ ጥቃት ሊያደርሱበት ሞክረው ሳይሳካላቸው ቀርቷል ፡፡ በተለይ ትናንትና ዛሬ ብዙ ተማሪዎችን ሲተናኮሉና ሲደባደቡ ነበር።
በዚህ አጋጣሚ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እርስበርሳችሁም ሆነ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጋር አፋጣኝ መረጃ ትለዋወጡ ዘንድ እንመክራለን።

Sunday 16 October 2016

ሰበር_መረጃ አስቸኳይ የፋይናንስ አዋጅ ሊታወጅ እንደሆነ ተሰማ

ሰበር_መረጃ….አስቸኳይ የፋይናንስ አዋጅ ሊታወጅ እንደሆነ ተሰማየብሔራዊ ባንክ ውጭ ምንዛሪ ካዝና ባዶ ነው

October 16, 2016

የኢህአዴግ ጽ/ቤት በትርምስና የእርስ በእርስ ውንጀላ ላይ ነው። በውጪ እና በሀገር ውስጥ ኢንቬስተሮች ከኤክስፖርት ይገኝ የነበረው የውጭ ምንዛሪ በ5 ወራት ውስጥ በ71.1 በመቶ በመቀነሱ ለመጀመሪያ ጊዜ የ1.9 ቢሊዮን ዶላር የገቢ ውድቀት ታይቷል። ከተጠበቀው በታች በመቀነሱ ይሄንን የህዝብ አገልግሎት ሰጪ የሆኑ የትምህርት ቤት በጀት (የመምህራን ደሞዝን ጨምሮ)፣ የጤና አገልግሎት፣ ትራንስፖርት፣ ከፍተና ወጪ ያስከተለው የፖሊስ ሰራዊትና የወታደሮች ደሞዝ በዚህ የበጀት ቀውስ ምክንያት በመስተጓጎሉ አዲስ አዋጅ ማስፈለጉ ተሰምቷል።

ከሁሉም አስከፊ የሆነው ከቻይና ሌሎች አበዳሪዎች ለኢንቨስትመንስት ጉዳይ ተብሎ የተገኘው ብድር 16 ቢሊዮን ዶላር በመድረሱ በመጀመሪያው የክፍያ በ2016 አመት አስከፊ የፋይናንስ ቀውስ መገባቱ ምክንያት ሆኗል። ኢትዮጵያ በአሳሳቢ የዕዳ ሽክም ከአለም 11ኛ ሆናለች። ከዚህ ባለፈ ለውድቀቱ ተጨማሪ ምክንያት የሆነው እርዳታ ሰጪ ሀገሮች በየጊዜው የሚያስገኙት የበጀት ድጋፍ እየቀነሰ በመምጣትና ወደ ሰብዓዊ አስቸኳይ የምግብ ርዳታ ላይ ትኩረት በማድረጋቸው መሆኑም ጭምር ነው።
http://www.satenaw.com/amharic/archives/23331

Monday 3 October 2016

የኢሬቻ በዓል ጭፍጨፋ

ፕሮፌሰር መስፉን ወ/ማሪያም
የኢሬቻ በዓል ጭፍጨፋ፡--- እንደሰው ያሳዝነኛል፤ ያሳፍረኛል፤ እንደኢትዮጵያዊ ዜጋ ያዋርደኛል፤ ያሳጣኛል፤ አለኝ የምለውን የጨዋነት ባህል፣ ይሉኝታና ክርስስቲያናዊ ሰብአዊነት ያጎድፍብኛል፤ ራቁቴን በዓለም ሕዝብ ፊት ያቆመኝ ይመስለኛል፡፡
ለሥልጣን ብዙ ሰዎች ሰዎችን አጫርሰዋል፤ ብዙ ንብረትን አውድመዋል፤ የብዙ ሕዝቦችን የእድገት እርምጃ አግደዋል፤ ወደኋላም መልሰዋል፤ ሞት እየቀጠፋቸው ሥልጣናቸው ባልወደዱት እጅ ገብቷል፡፡
ለሀብት ብዙ ሰዎች ሰዎችን አጫርሰዋል፤ ከሰው ልጅ ሕይወት፣ ከሰው ልጅ ምቾት ሀብት በልጦባቸው ጤንነታቸውን እያጡ በማያሸንፉት ሞት ተቀጥፈዋል፤ ከሰው ልጅ የበለጠባቸው ሀብት እንኳን ለነሱ ለልጆቻቸውም ሳይሆን ተዝረክርኮ ቀርቷል፡፡
የባለሥልጣንና የሀብታሞች ሎሌ በመሆን ወንድም ወንድሙንና እኅቱን ገድሎ፣ ጎረቤቶቹንና ወገኖቹን አስቀይሞ ከውርደት ኑሮ በቀር ክብርንና ኩራትን አያገኝም፤ የሠራውን ሥራ፣ ወንድሙን ወይም እኅቱን መግደሉን፣ ከእሱ በቀር የሚያውቀው የለም ይሆናል፤ ይህ አእምሮውም ውስጥ ልቡም ውስጥ የተለጠፈ እውቀት በመቃብርም ሆነ ከመቀብር ውጭ አይለየውም፤ ማናቸውንም ምቾት ይነሳዋል፡፡
መግደልም ሆነ ማስገደል የመጨረሻው የውድቀትና የጻዕር ምልክት ነው፤ ወይም የታቀደ የመጨረሻው እልቂት መጀመሪያ ነው፤ የተጠቂው ወገን ሲመርረው አጥቂው ካልጎመዘዘው፣ አጥቂው እስቲጎመዝዘው ድረስ የተጠቂው ምሬት ቋቅ እስቲለው ይቀጥላል፤ የተጠቂው ምሬት ቋቅ የሚያስደርግ ደረጃ ላይ ሲደርስ የአጥቂውም መጎምዘዝ ወደምሬት ያሸጋገራል፤ ትእግስት የጎደለው የአጥቂ ጉልበተኛ ምሬትና ቋቅ የሚል የተጠቂ ምሬት ሲጋጠሙ ውጤቱ እልቂት ነው፤ ጉልበተኛ ጉልበቱ እስቲሰበር የሞተ ኅሊና (እንጉርጉሮ ወይም አሁንም እንጉርጉሮ) በሚለው ግጥሜ በከፊል የሚከተለውን ብዬ ነበር፡---
ከሳሽ፣ ተከሳሽ፣ ዳኛ መሆን
እንዴት ይችላል መበየን?
ሲፍነው ግን ኅሊናውን፣
አይለይም ጨለማውን ከብርሃን!
ኅሊናውን የገደለ ሰው
ማን ሊቀረው? ምን ሊያቅተው?
የጉልበቱ መሣሪያ ነው፤
ጊዜ ጉልበቱን እስቲሰብረው!
እግዚአብሔር ከመጨካከን ፉክክር ይጠብቀን፡፡

Friday 2 September 2016

#ኮንሶ #አርባምንጭ

Breaking News
    #ኮንሶ
    #አርባምንጭ
 ህዝባዊው ንቅናቄ ወደ ደቡብም እየገባ ነው። በኮንሶ እና አርባምንጭ ለሦስት ቀን ከቤት ያለመውጣት ተቃውሞ
ተጠርታል በዚህ ተቃውሞ መላው የኮንሶ የአርባምንጭ ህዝብ ከወገኑ የአማራና የኦሮሞ ህዝብ ጎን መቆሙን የሚያሳይበት ነው ተብሏል። የከተማው ወጣቶች የወያኔን ገዳይ ስርአት በመቃወም የሚታወቁ ሲሆን በዚህም ቂመኛው የወንበዴ ቡድን በከተማው ነዋሪ ላይ ከፍተኛ ግፍ መፈፅማቸው ይታወቃል አርባምንጭ ይለያል ዘንድሮ የወያኔ ኑሮ ያሉ ነው።

Wednesday 31 August 2016

Ethiopian regime deploying massive military to the Amhara region as uprising continue unabated

Ethiopian regime deploying massive military to the Amhara region as uprising continue unabated
By Engidu Woldie
ESAT News (August 31, 2016)
Reports reaching ESAT from Ethiopia say the TPLF regime is deploying thousands of its troops and Agazi Special Forces to the Amhara region where uprising against the regime is gaining momentum as more towns and localities removed local administrations and the security, and replaced them with interim administrations elected by the people.
Thousands of troops in a dozens of convoys and heavy machinery were seen heading towards northern Gondar via Wuchale, Wollo as the alternative and direct routes were closed by protesters, according to a sources who spoke to ESAT.
ESAT is yet to verify the information but high ranking TPLF military and civilian officials led by chief of staff Samora Yunis have arrived in Gondar. Close observers of the new developments say the regime was heading towards forming military posts and putting in place a military administration as seen in the Oromo region of the country where a nine month protest has relatively quieted this month.
Deadly protests have however continued on Tuesday in Gondar and Gojam where seven protesters - three in Adet and four in Simada - were shot and killed by TPLF forces. Three people were also killed in Merawi.
In Bahir Dar, angry protesters went to the Sebatamit prison and freed 700 prisoners who were detained in the recent protests. Several people were injured in the shoot out to free the prisoners, according to hospital sources. Gun fire could be heard on Tuesday in the city of Bahir Dar which saw deadly protests on Monday as four people were killed and protesters attacked businesses belonging to the regime.
In Amba Giorgis, regime forces attacked residents who on Monday targeted businesses and set on fire houses belonging regime officials.
Tensions remained high in Fnote Selam that has seen deadly protests in recent days. Offices and businesses remained closed on Tuesday in Finote Selam.
Prime Minister Hailemariam Desalegn blamed the unrest on what he called “foreign forces” bent on distracting the country from its development and fomenting ethnic conflicts. He declined to name the “foreign forces” but went on to accuse them of providing financial support to Ethiopian opposition forces in the diaspora.
The Premier’s accusations did not come as a surprise to political observers who said that it has been customary for the regime to blame external forces for all its internal crises.
Meanwhile, human rights groups called for an independent investigations into the killings and incarceration of civilians by security forces in Ethiopia. Defend Defenders, Amnesty International, Ethiopian Human Rights Project, Frontline Defenders and FIDH called in a joint statement for the immediate cessation of the killings and detention of peaceful citizens and members of the civic society.

Friday 22 July 2016

ህወሓት አማራ ቴሌቪዥንን ዘጋ

ሰበር ዜና
ህወሓት አማራ ቴሌቪዥንን ዘጋ፡፡
ህወሓት በአማራ ክልል መንግስት ከመናደዱ የተነሳ እሱ በሚቅጣጠረው ቴሌ አማካኝነት የቴሌቪዥን ጣቢያው ከናይል ሳት እንዲቋረጥ አድርጓል፡፡ እንደ አማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ገለፃ ከሆነ ምክኒያቱ ከዚህ በታች የተጠቀሰው ነው፡-
የአማራ ቴሌቪዥን በናይል ሳት ሳተላይት ስርጭቱን ለተመልካቹ እንደሚያደርስ ይታወቃል፡፡ የሳተላይት ክፍያው ለመፈፀም ደግሞ የአማራ ብዙሃ መገናኛ ድርጅት ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በወቅቱ ይከፍላል፡፡ ኢብኮ ደግሞ ለኢትዮ ቴሌኮም ክፍያውን ያስገባል፡፡ በዚህ ሂደት ላለፉት 2 አመታት የተፈፀመውን ክፍያ ኢትዮ ቴሌኮም ለሳተላይት አከራዩ ድርጅት ባለመክፈሉ የአማራ ቴሌቪዥን ስርጭቱ ዛሬ ንጋት ጀምሮ ተቋርጧል፡፡ ይላል፡፡ ሆኖም አሁን ላይ መሆኑ የጎንደሩን ጉዳይ አሸባሪ ምናምን እያለ እንደ ህወሓት ባለማስጮሁ ተበሳጭተው እድርገውት ይሆናል፡፡ ህወሓት የአማራ ክልል መንግስትን ውስጡ ገብታ መፈረካከስ ቢያቅጣት ብቸኛውን የአማራ ቴቬ ዘጋችው!
የፌደራል መንግስቱን መጠቀሚያ በማድረግ አማራ ክልልን ማጥቃት ቀጥላለች፡፡ የሚገርመው ከመንግሥት ሚዲያዎች አማራ ቴቪ ነበር የምመለከተው፡፡ ለጊዜው ሌላ አማራጭ አያለሁ፡፡ ፈቅደው ከከፈቱላቸው ሃሃሃሃ ገና ብአዴንና ህወሓት ወደ ጦርነት ሳይገቡ አይቀርም በዚህ አያያዝ፡፡ ምክኒያቱም የህወሓት ጥጋብና ትዕቢት ወሰን አጥቷልና፡፡ ነገ ደግሞ ምን ሊዘጉ ይሆን?
የድጎማ በጀት?

Friday 10 June 2016

ዳባት አመረረ ውጥረቱ አይሏል

ዳባት አመረረ ውጥረቱ አይሏል! ነገሩ ከቁጥጥር ውጪ እየሆነ ይገኛል። የጎንደር ህዝብ ተማሯል በወልቃይት ጠገዴ ዳንሻ አርማጮሆ ቃብቲያ የነበረው ቁጣ አሁን ወደ ዳባት እየዘመተ ነው፡፡ በዳባት የህዝቡ ምሬት አስፈሪ አድርጎታል፡፡ ተነቅሎ ሊወሰድ የነበረው አላስነካም ማለቱ ዳባት እንደቀድሞ አይደለችም፡፡ ገበሬው ሳይቀር የከተማው ነዋሪ ጡሩንባ እየነፋ የክተት ጥሪ አውጇል፡፡ ትንሽ ትልቁ ሁሉም ነቅሎ በመውጣት ቁጣው አደገኛ ደረጃ ደርሷል፡፡ መንገድ ተዘግቷል የአስተዳር ፅ/ቤት ተቋረጠ ለስብሰባ የመጡ የመንግስት ባልስልጣናት በዱላና ድንጋይ አባሯል፡፡ ዳባት በዚህ ሰዓት በፌደራል ፖሊስ ከተማዋ እየታመሰ መሆኑ #በኢሳት ራዲዮ እየተሰማ ነው፡፡ ነዋሪው በቃ.መሮናል ከዚህ በላይ አንፈልግም አንገሸገሸን በማለት እንደ ቃብቲያ ቆርጦ መነሳቱ በዳባት ውጥረቱ እየተገለፀ ይገኛል። ጉድ በል ዳባት !!

Thursday 9 June 2016

Breaking news

የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የክልሉ የግብርና ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ጀማነህ ታሰሩ
የቀድሞው የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባልና የክልሉ የግብርና ቢሮ ኃላፊ በዛሬው ዕለት አስቸኳይ ስብሰባ ባደረገው የጨፌ ኦሮሚያ ያለመከሰስ መብታቸው እንዲነሳ ከተደረገ በኋላ በደብረ ዘይት በክልሉ ፖሊስ በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ተደርጓል። ዘላለም ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀም የግል ሀብታቸውን በህገወጥ መንገድ ሲያካብቱ መቆየታቸውን የክልሉ የፀረ ሙስና ኮሚሽን ማስታወቁን ፋና አትቷል ።

Wednesday 8 June 2016

11% economic growth Vs reality in Ethiopia

እነዚህ ፎቶዎች የተነሱት በባህርዳር ከተማ ድባንቄ መድሃኒያለም ቤ/ክ አካባቢ በሚገኝ የአትክልት የቆሻሻ መድፊያ ቦታ ላይ  ነው። ከሰቆጣ በድርቁ ምክንያት የተሰደዱ ዜጎች ከእንስሳቱ ጋር እየተጋፉ የማንጎ ትራፍራፊ ሲለቅሙ ይታያል። ፎቶዎችን ለላኩልን ወገኖች ምስጋናችንን እንገልጻለን።

ሰበር ዜና ( breaking news)

ዳባት ዛሬ በተኩስ ስትናወጥ ዋለች። የከተማዋን ትራንስፎርመር ነቅለው ወደ ትግራይ ክልል ለመውሰድ የተደረገውን ሙከራ ህዝቡ እርምጃ ወስዶበታል። ትራንፎርመሩን የጫነው ከባድ ተሽከርካሪ ተቃጥሏል። ዳባት ማምሻውንም በውጥረት ላይ ነች። መንገዶች ተዘግተዋል። የከተማው ታጣቂ ሃይል ከአቅሙ በላይ በመሆኑ ፌደራል ፖሊስ ገብቷል።

Tuesday 7 June 2016

አቶ ሃብታሙ አያሌው በእስር ቤት የገጠመውን ልብ የሚነካ ሁኔታም ተናግሯል::

በቅርቡ ከእስር የተፈታው የቀድሞው አንድነት ፓርቲ አመራር አቶ ሃብታሙ አያሌው እስር ቤት እያለ በደረሰበት እንግልት በደረሰበት ህመም የተነሳ ለህክምናው ወጪ በሚል በዘ-ሐበሻ አዘጋጆች አስተባባሪነት በድረገጽ; በአዲስ ድምጽ ራድዮና ሕብር ራድዮ ድጋፍ የገንዘብ ማሰባሰብ ተደርጎ ነበር:: ኢትዮጵያውያን ይህን ጥሪ ከመላው ዓለም ተቀብለው $23,344 በኢንተርኔት አዋጥተው ለሃብታሙ አያሌው ጤናው እንዲመለስለት ተመኝተዋል:: ሃብታሙ የተዋጣለትን ገንዘብ ሰሞኑን ከተቀበለ በኋላ ከሕብር ራድዮ ዳይሬክተር ሃብታሙ አያሌው ጋር ልዩ ቃለምልልስ አድርጎ ሕዝቡን አመስግኗል:: በእስር ቤት የገጠመውን ልብ የሚነካ ሁኔታም ተናግሯል:: ያድምጡት – ሼር ያድርጉት::
http://www.zehabesha.com/amharic/archives/61743

Tuesday 24 May 2016

የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር ዶ/ር ታደሰ ብሩ ከአሜሪካን ሀገር የተለያዩ ሴነተሮችና ባለስልጣናት ጋር በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ።

የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር ዶ/ር ታደሰ ብሩ ከአሜሪካን ሀገር የተለያዩ ሴነተሮችና ባለስልጣናት ጋር በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ።
ዶ/ር ታደሰ ብሩ ለአጭር ጊዜ ጉብኝት አሜሪካን ሀገር የሚገኙ ሲሆን፤ በቆይታቸው ወቅት በኢትዮጵያ የሰባዊ መብት፣ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር ዙሪያዎች ከአሜሪካን ኮንግረስማን ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በተለይም ከከሎራዶው ኮንግረስማን ማይክ ኮፍማን ጋር በወቅታዊ እና ዘላቂ መፍትሄዎች ላይ አመርቂ ውይይት ማድረጋቸው ተገልጾል።

ኮንግረስማን ኮፍማን ዶ/ር ታደሰን ስለ ኤርትራ ቆይታቸው ምን እንደሚመስል ጠይቀዋቸው፡- ዶ/ር ታደሰም ሲመልሱ፡- በህወሃት መንግስት የሚደረገው ህዝብን የማጣላት፣ በኢትዮጵያና ኤርትራ ህዝበ መካከል በጠላትነት እንዲተያዩ የሚያደርገው ዘመቻ የተሳሳተ መሆኑን ገልጸው አርበኞች ግንቦት 7 ዘላቂ ወዳጅነትን እየጠናከረ እንደሚገኝ እና የሁለቱ ህዝብ ጠላት TPLF እንጂ ሌላ መሰረታዊ ችግርች እንደሌሉ እና ለኤርትራ ህዝብ ያላቸውን አድንቆት በመግለጽ አብሮ መስራት እንደሚቻል ያላቸውን እምነት ገልጸውላቸዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ የምትከተለውን የውጪ ፖሊሲዋን እንደገና እንድትመረምረውም አሳስበዋል።  አያይዘውም ኮንግረስማን ማይክ ኮፍማንና ሌሎች ሴነተሮች በቅርቡ በሜሪላንዱ ሴነተር ካርደን ቤንጃሚን ተረቆ የቀረበውን Resolution 432 በርካታ ሴነተሮች የፈረሙበትን የኢትዮጵያ ሰበአዊ መብትና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ድጋፋቸውን ይሰጡ ዘንድ ኮንገርሰማኑን ጠይቀዋል።

በመጨረሻም ኮንግረስማን ማይክ ድርጅቱ በሁለቱ ሀገራት ህዝብ መካከል እየፈጠረ ያለውን የሰላም ድልድይ እና የማቀረረብ ሂደት አድንቀው፤ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ጉዳዮችም እንደሚከታተሉ ገልጸውላቸዋል።
Abbay media

ሰበር ዜና.. ጌታቸዉ አሰፋ ስብሰባ አቋር ጦ ወጣ

ሰበር ዜና..
ጌታቸዉ አሰፋ ስብሰባ አቋር ጦ ወጣ..
በትናንትናዉ እለት የወያኔ ተላላኪ ከሆኑት እና ከብሔራዊ መረጃ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ካላቸዉ ግለሰቦች መካከል አምባሳደር ቀጸላ ከብሀራዊ መረጃዉ ሐላፊ ከጌታቸዉ አሰፋ ጋር አርበኞች ግንቦት 7 በአርባ ምንጭ ላይ የወሰደዉን እርምጃ ተንተርሶ ዉይይት በሚያደርጉበት ወቅት በተመሳሳዩ በደቡብ ኢትዮጵያ ኮንሶ አካባቢ በትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ተፈስሞ ከ 55 በላይ የሚጠጉ የፖለቲካ እስረኞች ማምለጣቸዉ 19 የወያኔ ታጣቂዎች መገደላቸዉና ቁስለኛ መሆናቸዉን የሚያበስር ዜና በስብሰባዉ ላይ የደረሰዉ ጌታቸዉ አሰፋ በአፋጣኝ ስብሰባዉን አቋርጦ መዉጣቱን ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።
አርበኞች ግንቦት 7 በፓርላማ ዉስጥ ሳይቀር መነጋገሪያ እርእስ መሆኑን የገለጹት ምንጮቻችን አክለዉ የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ የፈጠረዉ ፖለቲካዊና ህዝባዊ ጫና እንዳለ ሆኖ በጎንደር አርማጭሆ ሁመራ እና በትግራይ ጎንደር አዋሳኝ በኡማህጅር አካባቢ ድንገተኛና አደገኛ ጥቃቶች መሰንዘራቸዉን እንዲሁም በ24 እና በ25ኛ ክፍለጦር ተዉጣጪ የጸረ ሽብር ሐይል ላይ በተደረገ ሽምቅ ዉጊያ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን መረጃዎች ጠቁመዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
(ጉድሽ ወያኔ)

Saturday 14 May 2016

በኢትዮጵያ ጥቃት ያደረስኩት እኔ ነኝ ሲል አርበኞች ግንቦት ሰባት ኃላፊነቱን ወስዷል

ሰሞኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ጥቃት ያደረስኩት እኔ ነኝ ሲል አርበኞች ግንቦት ሰባት ኃላፊነቱን ወስዷል። የድርጅቱሊቀ መንበር ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ ከዝግጅት ክፍላችን ጋር ባደረጉት አጭር ቆይታ፥  "ትግላችንን የምናካሂደው እዚያው ኢትዮጵያ ውስጥ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ሆነን ነው" ብለዋል። የኤርትራ መንግሥት አሰልጥኖ የላካቸውን አሸባሪዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና የፌዴራል ፖሊስ ፀረ-ሽብር የጋራ ግብረ ኃይል ማስታወቁ ይታወቃል።

Monday 2 May 2016

በቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኘው ወጣት አባይ ዘውዱ ሕይወቱ አዳጋ ላይ መድረሱ ታወቀ፡፡

ከሰሜን ጎንደር ታፍኖ በቂሊንጦ የስቃይ ማጎሪያ የሚገኘው የቀድሞ ኣንድነት ፓርቲ ኣመራር ወጣት ኣባይ ዘውዱ በእስር ቤት ሕይወቱ ሊያልፍ እንደሚችል በከፍተኛ ሰጋት ላይ ወድቋል፡፡ ኣባይ ዘውዱ በደረሰበት የጉበት እና ጣፊያ እብጠት ሊፈነዳ ሲሆን በተጨማሪም በቲቪ-በከፍተኛ ደረጃ መታመሙ በደረሰን ጥቆማ ዛሬ 22/08 ቂሊንጦ በመሄድ ከራሱ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ወጣት ኣባይ ዘውዱ በህመሙ ሰውነቱ ኣልቆ በሰው ተደግፎ እያቃሰተ ማየት ያማል፡፡  የተሟላ ህክምና እንደተከለከለ ኣባይ እንባውን እያፈሰሰ ይናገራል፡፡ ይህ ለመላው ኣገር ወዳድ በተለይ የኣማራ ሕዝብ በዝምታ ተመልክቶ የወጣት ኣባይ ዘውዱ ሕይወት ልናጣው ከቻልን ለኣማራ ሕዝብ ትልቅ ውድቀት ትልቅ ዋጋ እንደሚያስከፍል መገንዘብ ያሻል፡፡ ኣባይ ዘውዱ-ሁለተኛ ድግሪውን ከቅርብ ጊዜ በፊት ያጠናቀቀ ሲሆን በከፍተኛ ትምህርት የቆይታውም ቢሆን ከባሕር ዳር ዩንቨርስቲ የማዕረግ ተመራቂ የነበረ ወጣት ምሁር ነው፡፡ ኣባይ ዘውዱ የቀድሞ ኣንድነት ፓርቲ ከተቀላቀለ በኃላ በነበረው ንቁ ተሳትፎ ከሚሰራበት ቦታ ከማባረር እንስቶ በኣካሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲደርስበት የቆየ ጠንካራ ጓዳችን መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተለይ ለሱዳን ሊሰጥ በታሰበው መሬት ዙሪያ ኣባይ ዘውዱ ከጎንደር ኣዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በኣንድነት ፅ/ቤት ሰፊ የዳሰሳ ጥናቱን ካቀረበ ወዲህ በወያኔ አይን እንደገባ ይነገራል፡፡ ለዚህ ጀግና ጓዷችን ኣገር ወዳድ ሊደርስለት ይገባል፡፡ ኣማራ ልጆቹን በዘረኞች እያስበላ የሚኖረው እስከመቼ ነው?
ወጣት አክቲቪስቶች የሚዲያ ኣካሎች በሙሉ ወጣት ኣባይ ዘውዱ የተሻለ ህክምና እንዲሰጠው ግፊት ማድረግ ሕይወቱን መታደግ ግዴታ ኣለበት፡፡ የነቃ ተሳትፎ ያላቸው የኣማራ ተወላጅ የሚደርሰው ዘር የማጥፋት ድርጊት ሊወገዝ ኣምሮ ሊታገሉት የሚገባ ተግባር ነው፡፡ ሁሉም ወገን ወዳድ ለኣባይ ዘዉዱ ድምፁን ያሰማለት፡፡ ኣማራ ነገ ታሪኩ ሲነገር ሊያፍርበት ይችላል፡፡

Saturday 9 April 2016

17 ዓመት ሙሉ መታኮስ ይኖራል ብላችሁ አትጠብቁ

ብዙ ሰዎች የጥይት ድምፅ ካልሰሙ ፣ ዛሬ በተደረገው ውጊያ ይሄን ያህል ሞተ ይሄን ያህል ቆሰለ የሚል ዜና ካልሰሙ እየተደረገ ያለው ትግል እውነት አይመስላቸውም። ወደዳችሁም ጠላችሁም ወያኔን በቁሙ የማፍረስ ስራ በሚገርም ሁኔታ እየተሰራ ነው። 2008 ከገባ በኋላ እንኳን በሀገሪቷ በአራቱም ማዕዘን አስገራሚ ህዝባዊ ንቅናቄን መፍጠር ተችሏል። ልክ እንደወያኔ 17 ዓመት ሙሉ መታኮስ ይኖራል ብላችሁ አትጠብቁ አሁን እየተሰራ ያለው ስራ ስርዓቱን በቁሙ የመግደል ስራ ነው። ስርዓቱ መሞቱ ከተረጋገጠ በኋላ የቀብሩ እለት ከባድ የተኩስ ልውውጥ ሊኖር ይችላል። ከዛ ባለፈ ረዥም ዓመታት የሚፈጅ የተኩስ ልውውጥና ብዙ ሕይወት የሚቀጠፍበት ነገር አትጠብቁ ምክንያቱም ትግሉ የሚመራው በተማሩ ሰዎች ስለሆነ።

Tuesday 5 April 2016

መክሸፍ ባሀል በመሆኑ ዛሬ ኢትዮጵያ በሁሉም ነገር ከአብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች በታቺ ነች፣

የዛሬ ትውልድ የቀዳማዊ ሀይለ ስላሴን ዩኒቨርስቲ ታሪክ አያቅም፣በአስራ ዘጠኝ ሀምሳዎቹ በአፍሪካ ውስጥ የሚወዳደረው ዩኒቨርስቲ አልነበረም፣ በምእራብ አፍሪካ ከናይጀርያና ከጋና ፣በምስራቅ አፍሪካ ከኬንያ፣ከታዛንያና ከዩጋዳ ነፃ ትምሀርት እየተሰጣቸው ይማሩ ነበር፣ ሮበርት ኡጎ የሚባለው የቀዳማዊ ሃይለ ስላሲ ምሩቅ የኬንያ የውጭ ጉዳ ምኒስተር ነበር፣ጆርጅ ማጎምቤየሚባለው የታንዛንያ ወጣት በሁዋላ በብዙ ሀገሮች በኢትዮጵያም ጭምር አምባሳደር እየሆነ ሰርቷል፣ የኢትዮጵያ አየር ሀይልም፣ የኢትዮጵያ አየር መገድም ለብዙ የአፍሪካ አገሮች የዘመናዊ እውቀትና ጥበብ ምጮች ነበሩ።መክሸፍ ባሀል በመሆኑ ዛሬ ኢትዮጵያ በሁሉም ነገር ከአብዛኛዎቹ የአፍሪካ አገሮች በታቺ ነች፣ ቁልቁል መውረድ ባሀል ሲሆንና ሀዝብ እሪ! ሳይል ሳይጮሀና ሳያለቅስ ገደል አፋፍ ላይ የደረሰ ይመስለኛል።
#ከአዳፍኔመፅሀፍገፅ22የተወሰደ።

Saturday 2 April 2016

የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ህልሞች- የኢሕዴግ ቆርጦ ቀጥል ፖለቲካ

የዶ/ር መራራ ጉዲና ምልከታ
በተቃዋሚ ጎራ፣ ብዙ ሳይንቀሳቀስ እያየሁ ያለሁት የኦሮሞና የአማራ ልሂቃን ፖለቲካ ነው። የሁለቱም ልሂቃን ፖለቲካ በዋናነት በሁለቱ ጫፎች ላይ ቆሞ ገመድ ከመጓተት ወደመሃል መጥቶ የጋራ ዴሞክራቲክ አጀንዳ መቅረጽ አላስቻለቸውም። ብዙዎቹ ሂሳብ የማወራረድ ፖለቲካን የዛሬ 30 እና 40 አመታት ብቻ ሳይሆን የዛሬ 130 እና 140 አመታት በፊት የነበረውም ጭምር የታሪክ ሂሳብ እንተሳሰብ የሚሉ ይመስሉኛል። የኦሮሞ ልሂቃን ዋናው ችግራቸው የጋራ የፖለቲካ አጀንዳ ለመቅረጽ ከመጣር ይልቅ ለብቻቸው የሚያደርጉትን ትግል የመንግስተ ሰማያት አስተማማኝ መንገድ አድርገው መምለካቸው ነው።
የአማራው ልሂቃን ዋናው በሽታቸው በዋናነት በአማራው ልሂቃን የተፈጠረችው ኢትዮጵያ በዋናነት እንደዛው ትቀጥል መቀጠለም ትችላለች የሚል ነው።
የሁለቱም ልሂቃን ያለፉት አርባ አመታት ጉዞ ሌኒን እንደሚለው "የሞኝ ሩጫ ፍጥነት አይጨምርም" አይነት ነው። በእኔ እምነት ሁለቱም ከታሰሩበት የታሪክ እስር ቤት ወጥተው በጋራ የዴሞክራቲክ አጀንዳ ላይ ተስማምተው በመሃል መንገድ ላይ ካልተገናኙ የኢትዮጵያ ፖለቲካ በአሁኑ ትውልድ ዘመን ፈቀቅ የሚል አይመስለኝም።
ዶ/ር መራራ ጉዲና
የኢትዮጵያ የታሪክ ፈተናዎች እና የሚጋጩ ህልሞች-የኢሕዴግ ቆርጦ ቀጥል ፖለቲካ

የትግራይ ድንበር እስከ ተከዜ ወንዝ ነዉ ብለዉ ያምናሉ የተባሉ....

ሰበር መረጃ . . ወያኔ በአርማጭሆ ዙሪያ የቤት ለቤት አሰሳ ሊያካሂድ መሆኑ ተሰማ!!
በወታደራዊ እምነቱ እየተመናመነ ዉስጥ ለዉስቱ እየተበላላ የመጣዉና የመጨረሻዉ ገደል ጫፍ ላይ የሚገኘዉ የወያኔ ስርአተ ቀብርን በማስፈጸሙ ስራ ላይ እየተጉ የመጡት የነጻነት ሐይሎችን ይረዳሉ፣ ያግዛሉ፣ መረጃ ይሰጣሉ እራሳቸዉን የዉስጥ አርበኞች ብለዉ እያደራጁ ነዉ ከጀርባቸዉ አርበኞች ግንቦት 7 አለ የተባሉ የ24ተኛ ክ/ጦር አመራሮች እየታደኑ ይገኛሉ።
የራሱ ጅራፍ እራሱን እየገረፈዉ የሚገኘዉ የትግራይ ነጻ አዉጭ ቡድን ከፍተኛ አመራሮች እየሸሹ ወደ ጎረቤት ሐገር ገብተዋል።
የዉስጥ አርበኞችን አድናለዉ ያለዉ የወያኔ ወታደራዊ ደህንነቱ የራሱን ቀንደኛ ሐይሎች በመብላቱ በመላዉ ሐገሪቱ እየተስፋፉ የሚገኙት የዉስጥ አርበኞች ደስታቸዉን ሲገልጹ ሰንብተዋል ! ! ! በመሆኑም ከዚህ ጋር በተያያዘ ለወያኔ አይታዘዙም፣ በወልቃይት ትግሬነት አይስማሙም፣ የትግራይ ድንበር እስከ ተከዜ ወንዝ ነዉ ብለዉ ያምናሉ የተባሉ የአርማጭሆ ገበሬዎችን ትጥቅ ለማስፈታት የቤት ለቤት አሰሳ እንዲደረግ የወያኔ ሹማምንቶች ተስማምተዋል በመሆኑም መላዉ የጎንደር ህዝብ ትጥቅህን እንድትጠብቅ በጥብቅ እናሳስባለን ትጥቅህ ክብርን የምታረጋግጥበት የመጀመሪያዉ ሐይል ነዉ ትጥቅ አስፈቺዎች ላይ እየወሰድክ ያለህዉን እርምጃ አጠናክረህ ቀጥል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
( ጉድሽ ወያኔ )

Friday 1 April 2016

ይች ሀገር የኢትዮጵያዊው ናት ወይስ እንደምናያት የባዕዳኖች ናት ።

ንብረትነታቸው የኢትዮጵያ የመንገዶች ባለስልጣን የሆኑና ዋጋቸው ከ65 ሚልዬን ብር በላይ 88 የኮንስትራክሽን ማሽነሪ ለጥገና ተብለው ወጥተው ከመስሪያ ቤቱ ወደትግራይ ተወስደው እንደወጡ ቀሩ ። መመለሱ ይድከማቸው ፣ ይደብራቸው ወይም መጋዘን ውስጥ ተነው ይጥፉ የታወቀ ነገር የለም ፣ ሁኖም ግን የመንገድ ባለ ሥልጣን የተባለው ማሽኖቹን ከወሰደው አካል መጠየቅ ባይችልም ከኢትዮጵያ ሕዝብ ንብረትነት እንዲሰረዙ የፌዳራል መንግሥት ከሚባለው የጠየቀ መሆኑ ተገልጿል ። እንደተባለው ወይም እንደተለመደው እንደ 10,000ቶን ቡና ለወደፊቱ እንዳይደገም ከተደገመም ለወደፊቱ እጅ እንቆርጣለን ተብሎ ይሆን አይታወቅም ። የኢትዮጵያ የሕዝብ ሀብት እንዲህ እንደዋዛ ያለምን ተቆጭ በተራ ዘራፊ እንዲህ ይወሰዳል ፣ ይች ሀገር የኢትዮጵያዊው ናት ወይስ እንደምናያት የባዕዳኖች ናት ።
ዜጋ የሚዋከብባት ዜጎች ከትውልድ መንደራቸው የሚባረሩባት ባዕዳን እንደፈለጉ የሚሆኑባት በግድ መሬት ውሰዱልን ወይም እንስጣችሁ ሱዳኖች የሚለመኑባት ሀገር
                   



Monday 28 March 2016

ሕወሓት ካድሬዎቿን ይዛ ወደ አፋር ክልል ለመስፋፋት #ሽኸት_ናብ_ትግራይ_ትመለስ ዘመቻ ጀምራለች::

ሕዝብ ለሕዝብ የሚያናክሰው የሕወሓት የመስፋፋት ፖሊሲ ተከዜን የወልቃይት እና ጠገዴን ምድር ከነሕዝቡ ወደ ትግራይ በማካለል በአከባቢው ከፍተኛ የፖለቲካ ቀውስ እንዲነሳ ያደረገ ሲሆን ቀውሱ እየተባባሰ ሕዝቡ መሳሪያውን እንደታጠቀ በዱር ሲገኝ በሽምግልና ለማዘናጋት እና ጊዜ ለመግዛት ሽምግልና አልቀመጥም ሲሉ በግዳጅ በዛቻ የሽምግልናው መሪ የሆኑት አንድ ጳጳስ ጨምሮ የተደረገው ሙከራ እንደተንጠለጠለ ይገኛል::#ሽኸት_ናብ_ትግራይ_ትመለስ የሚለው ዘመቻ የአፋር ክልል ወረዳዎችን በሙሉ ከጥንት ጀምሮ የትግራይ መሬዎች ናቸው የሚል እደምታ ይዞ ተጀምሯል::

እንዲሁም በቅማንት ሕዝብ አከባቢ እየተደረገ ያለው ሕዝብን የማጨፋጨፍ እና የመጨፍጨፍ ስራ በተክል ድንጋይ እንዲፈነዳ የተደረገ ሲሆን የውልቃይት ሕዝብን ጥያቄ ለማድበስበስ እና ለጊዜ መግዣ የሚደረጉ ሕወሓታዊ ተኮሎች ቀጥለዋል::አስተዳደራዊ ጉዳዩን መቀሌ እየመጣ እንዲያስፈጽም እየተደረገ ያለው የቅማንት ሕዝብን ወደ ትግራይ ጠቅልሎ እስከ ጎንደር መግቢያ ድረስ ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት እስካሁን ሊሳካ አልቻልም::ለዚህ ስራ የሚረዱ የሕወሓት ሚሊሻዎች እና የጦር መሳሪያዎች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እየተንጠባጠቡ በአከባቢው ሰፍረዋል::ሕዝቡን ይህንን በማወቁ መሳሪያውን ወልውሎ በተግባር እየተንቀስቀሰ ለሕወሓት ጦር የእግር እሳት ሆኖበታል::

ይህንን የአማራ ክልልን ሰነጣጥቆ የራሱን ግዛት ለማስፋፋት የሚመኘው የሕወሓት አገዛዝ የሱዳን ድንበርን ይዞ ከኩምሩክ ጀምሮ እስከ ሁመራ ድረስ የጉምዝ ተወላጆችን እና የሕወሓት ሚሊሻዎችን በማስፈር አስፈላጊውን እየሰራ ሲገኝ በአፋር ክልል ደግሞ ለመስፋፋት ያለውን እቅድ ለማሳካት #ሽኸት_ናብ_ትግራይ_ትመለስ የሚል አዲስ ዘመቻ በካድሬዎቹ እና በአሽቃባጭ ዘረኛ አማሳኞቹ በኩል ዘመቻ መጀመሩን ታውቋል::ይሕው ዘመቻ ተያይዞ የአፋር ክልል ሕዝብን አሳዶ ግዛቱን በማስፋፋት አከባቢዎቹን ከትግራይ ክልል ጋር ለመቀላቀል ነው::ይህ #ሽኸት የተባለ ቦታ ከጥንት ጀምሮ የትግራይ መሬት ነው ለስራ ጉዳይ አፋር ክልል የገቡ መሬትች ስለሚገኙ ከትግራይ ካልተቀላቀለ በትግሪኛ ትምሕርት ካልተሰጠ አፋርና አከባቢው ላይ መነገር ካልቆመ ለትግራይ ትልቅ ችግር አለ በማለት ሕወሓት እና ካድሬዎቹ እያራገቡ ነው::

መቀሌ ላይ ከሀሙስ ጀምሮ እስከ ትላንት ድረስ የተካሄደው ሚስጢራዊ ስብሰባ ምን ይሆን?

መቀሌ ላይ ከሀሙስ ጀምሮ እስከ ትላንት ድረስ የተካሄደው ሚስጢራዊ ስብሰባ ምን ይሆን? ሾልከው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ህወሀቶች የወልቃይቱንና የድንበሩን ጉዳዮች በቅማንት የማንነት ጥያቄ ለመቀልበስ እየመከሩ ነው። በዚህ ሚስጢራዊ ስብሰባ ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ጨምሮ ከተለያዩ ቦታዎች የተጋበዙ የትግራይ ምሁራን ተገኝተዋል። ወጣቶችም ተሳትፈዋል። አባይ ወልዱና ቁልፍ የህወሀት የደህንነትና ወታደራዊ ሰዎች ነበሩ። በአማራ የተጀመረው ንቅናቄ በደንብ እግር አውጥቶ ከመራመዱ በፊት መስበር ስለሚቻልበት ሁኔታ ሲመክሩበት ነበር። ለአሁን የቅማንትን የማንነት ጥያቄ ወደለየለት የእርስ በእርስ ግጭት መቀየር የሚለው ሀሳብ ተቀባይነት አግኝቷል።

Sunday 27 March 2016

የሕወሓት የመስፋፋት እቅድ የወለደው የእርስ በእርስ ጦርነት በተክል ድንጋይ ፈንድቷል::

Mereja
ከትላንትና ጠዋት ጀምሮ የሚደርሱ መረጃዎችን ተከትሎ ለማረጋገጥ እንደተቻለው የሕወሓት የመስፋፋት ፖሊሲ እና ታላቋን ትግራይ የመመስረት አላማውን ለማሳካት ሲል የሚሰራቸው እኩይ ተግባራት በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈራው የእርስ በእርስ ጦርነት በጎንደር ክፍለሃገር ተክል ድንጋይ መፈንዳቱን ከአከባቢው የተገኙ መረጃዎች ጠቁመዋል::ሕወሓት የቅማንት ሕዝብን ለእኩይ ተግባሩ ሊጠቀምበት በማሰብ ከፍተና የሆነ የጦር መሳሪያ እያስገባ ነው የሚሉ የተክል ድንጋይ ነዋሪዎች ይናገራሉ::በአምቡላስ ላይ የደረሰን የፈንጂ አደጋ ተከትሎ ከትላንትና ጀምሮ በሕወሓት የጦር ሰራዊት እና በጎንደር ክፍለሃገር ሕዝብ መካከል ግጭቶች ወደ ተኩስ በመለወጣቸው አከባቢውን የጦር አውድማ አድርገውታል::

በትላንትናው እለት በትክል ድንጋይ በአምቡላንስ ላይ የፈንጂ ጥቃት ደርሶ በአምቡላንሱ ውስጥ የነበሩ ሁለት ሲገደሉ በአንዱ ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሶ የነበረ ሲሆን የአከባቢው ሕዝብ ለአደጋው የሕወሓትን ሰራዊት ተጠያቂ አድርጓል::እንዲሁም ሁለት ታዳጊ ወጣቶች በሕወሓት ጦር መገደላቸውን የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ::ወደ ተክል ድንጋይ የሚያስገቡ መንገዶች የተዘጉ ሲሆን የሕወሓት ጦር በአከባቢው ውጥረት በመፈጠሩ መሳሪያ ያልታጠቁ ነዋሪዎች ራሳቸውን ከሕወሓት ጦር ለማዳን ወደ ጎረበት ወረዳዎች እየሸሹ ይገኛሉ::መሳሪያ የታጠቁ የተክል ድንጋይ ነዋሪዎች ከወያኔ ጦር ጋር እየተታኮሱ ይገኛሉ:: 

7 የሕወሓት ባለ ስልጣናት ባአማራ ክልል ሌላ ሴራ ጠንስሰዋል

ሚስጢራዊ መረጃ
የማስጠንቀቃያ ደውል ለአማራ ኢትዮጵያ በሙሉ
============%================
7 የሕወሓት ባለ ስልጣናት ባአማራ ክልል ሌላ ሴራ ጠንስሰዋል ፡፡
==> ወልቃይት ዳንሻ ላይ የተለኮሰውን የማንነት ጥያቄ ለማቀዝቀዝ ሌላ መንገድ ቀይሰዋል ፡፡
==> የሕወሓት መሀከላዊ ከሚቴ አባል የሆነው " አቶ ተክለ ወይኒ አሰፍ እና አስፋው ምሀሪ በሚባል የደህንነት አባል የሚመራ የኦሮ በላ ቡድን ተቋቁሟል ፡፡
==> ለነዚህ ኦሮ በሎች የተሰጣቸው ተልዕኮ የሚከተለው ነው ፡፡
1 ኛ አማራ ክልል ላይ ያሉ የተራድኦ ድርጅቶችን መዝረፍ ፡፡
2 ኛ ከሁመራ ሰሊጥ እና ቦሎቄ የጫኑ መኪኖችን መዝረፍ፡፡
3ኛ ቤተ ክርስቲያን እና የህዝብ መገልገያዎችን መዝረፍ እና ማውደም ፡፡
4 ኛ የአማራ ተወላጅ ሁነው  በመንግሥት ሥራ የተሰማሩ
ነገር ግን ስራቱን የማይደግፉትን " በሥራቸው ምክንያት ህዝብ የገደላቸው በማስመሰል መግደል ይላል የተሰጣቸው ተልዕኮ ፡፡ ባጠቃላይ አማራ ክልል ላይ ትልቅ ቀውስ መፍጠርን አላማ አድርጓል ፡፡
=> እነዚህ ችግሮች በመፍጠር የህዝቡን ስሜት በመክፈል ለጊዜውም ቢሆን ወልቃይት እና ዳንሻ ላይ ያለውን አመጽ ለማቀዝቀዝ ነው ፡፡
=> ከዚህም ጉንለጎን ወልቃይት እና አጎራባች አካባቢ ያለውን የህዝብ ንብረት ወደ መቀሌ ለማጓጓዝ ጊዜ ለማግኘት መሆኑ ታውቋል ፡፡
==> ስለዚህ ሁሉም የአማራ ህዝብ በያለበት በተጠንቀቅ ሊቆም ይገባል ፡፡ የዚህ አይነት ችግር ሲፈጥሩ የተገኙ ወዲያውኑ እርምጃ ይወሰድባቸው !!! አማራም ይሁኑ ትግሬ ወይም የሊላ ብሔር ፡፡
=> ማንም ይሁን የተወጣለትን አላማ ወደ ጉን ትቶ በዚህ ስራ ከተገኘ ወዲያውኑ እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል ፡፡
=> ምክንያቱም የአማራ ወጣቶች እና የህዝቡ ፋላጉት ንብረት ማውደም እና መዝረፍ አይደለም ፡፡ የማንነት ጉዳይ እንጂ ፡፡