Tuesday 30 June 2015

Why Pr Obama ignore the fact?

I'm sure Mr President won't say that, you don't know about TPLF's crime. in-case you do,  i attaches some links below for you. 
Genocide of Amaras
According to the 2007 Ethiopian population census 2.4 million Amaras have vanished (14%) of the total Amaras population. and  re checking process took 6 month, after 6 months Central Statistical Agencey Director Samiya Zekaria reported to PARLIAMENT the census report on Amara people was accurate. She proved that 2.4 million Amaras have vanished without a trace.There is only one way to view the census report.The Amara people have been systematically exterminated, THIS IS A GENOCIDE. 
The consequences of the census report TPLF cut the Amara region budget by the size equivalent to 2.4 million people.
for more watch;  https://www.youtube.com/watch?t=28&v=WpUxU5suuLs  


Massacre of Anuak, Gambella

December 13th Massacre of 424 disarmed Anuak in Gambella, Ethiopia eyewitness
https://www.youtube.com/watch?v=x_9aoVLNCA4  
https://www.youtube.com/watch?v=AQBTpVMLy7k  many more.......

journalist, activist, blogger, opposition party members and leaders, religious and so on are detained with fabricated history 
and recently 5 opposition party members and leaders are murdered by your alliance TPLF agents. 
and there are dozens of reports from Amnesty, Human Right Watch ,CPJ and even from USA annual report.
So here is my question
What Saddam Hussein or Muammar Gaddafi  have done to be targeted by your government? 







Saturday 20 June 2015

የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ከሳሙኤል አወቀ ለቅሶ እንዳይደርሱ ታገዱ

የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ከሳሙኤል አወቀ ለቅሶ እንዳይደርሱ ታገዱ• ከአዲስ አበባ ወደ ጎጃም ለሌላ ለቅሶ በመሄድ ላይ የነበሩ ዜጎች ተደብድበው ተመልሰዋል
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር የሰማያዊ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ሰኔ 8/2007 ዓ.ም ደብረማርቆስ ከተማ የተገደለው የሳሙኤል አወቀ ለቅሶ እንዳይደርሱ ታገዱ፡፡ አመራሮቹና አባላቱ ዛሬ ሰኔ 13/2007 ዓ.ም በጠዋት ከአዲስ አበባ ተነስተው የሳሙኤል አቀወ ቤተሰቦች ወደሚገኙበት ምስራቅ ጎጃም ዞን ግንደወይን እያቀኑ በነበረበት ወቅት አባይ ድልድይ ላይ በፌደራል ፖሊስ ታፍነው ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ጎሃ ፂዮን ከተማ ውስጥ እስከ ምሽቱ 2 ተኩል ድረስ ታግተው ውለዋል፡፡ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላትን ወደ ለቅሶ እንዳይሄዱ ያገዱት ከአዲስ አበባ የሄዱና ከቦታው ተዘጋጅተው ሲጠብቁ የነበሩ የፌደራል ፖሊሶች እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡
አመራሮቹና አባላቱ ለፖሊስ ቃል ሲሰጡ ከሳሙኤል አወቀ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት፣ በፓርቲው ውስጥ ያላቸውን ኃላፊነት፣ ሳሙኤልን ማን እንደገደለው የሚመለከቱ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል፡፡ ለቅሶ እንዳይደርሱ ከተከለከሉትና ታተው የዋሉት
1. ኢ/ር ይልቃል ጌትነት/ የፓርቲው ሊቀመንበር
2. ይድነቃቸው ከበደ/ የፓርቲው የህግ ጉዳይ ኃላፊ
3. ወሮታው ዋሴ /የፓርቲው የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ
4. ሀብታሙ ደመቀ/ የኦዲትና ኢንስፔክሺን አባል
5. ጌታቸው ሺፈራው/ የነገረ ኢትዮጵያ ዋና አዘጋጅ
6. ጋሻው መርሻ/ የብሄራዊ ምክር ቤት አባል
7. እምላሉ ፍስሃ/ የብሄራዊ ምክር ቤት አባል
8. ሜሮን አለማየሁ/ አባል
9. ጥላሁን አበጀ/ አባል
10. ጠና ይታየው/ አባል
11. እስጢፋኖስ በኩረጽዮን /አባል
12. ኃይለማሪያም ተክለ ጊዮርጊስ/ አባል
13. ጋሻነህ ላቀ/ አባል
14. ግርማ ቢተው አባልና
15. የመኪናው ሾፌር ናቸው
ከምሽቱ 2 ሰዓት ተኩል ከአዲስ አበባ በመንገድ ትራንስፖርት ሰራተኞችና ትራፊክ ፖሊሶች ህጋዊ መሆኑ ተረጋግጦ ያለፈው እንዲሁም ለአራት ቀን ከፓርቲው ጋር ውል የያዘው መኪና እንዳይንቀሳቀስ ተከልክሎ ከፍተኛ አመራሮቹና አባላቱ ከእስር ተለቀዋል፡፡ በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ ልዑካን ይዘዋቸው የነነበሩ ቁሳቁሶች ለምርመራ በሚል በፖሊስ ተይዘዋል፡፡
በሌላ ዜና ከአዲስ አበባ ተነስተው ምስራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ኤልያስ ወደ ሌላ ለቅሶ ሲሄዱ የነበሩ ዜጎች የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ከታፈኑ በኋላ ደጀን ላይ ተይዘው ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞባቸው በግዳጅ ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ ተደርገዋል፡፡ ተመልሰው ወደ ለቅሶው ቢሄዱ እስከ 10 ሺህ ብር ሊቀጡ እንደሚችሉ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል፡፡ እነዚህ ዜጎች በተያዙበት ወቅት ሰማያዊ ፓርቲ ደብረማርቆስና ባህርዳር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ ሊያደርግ እንደሆነ እንደተገለጸላቸው እነሱም የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ ላይ ትገኛላችሁ ተብለው ተጠርጥረው እንደሆነ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ይህ ዜና እየተሰራ ባለበት ወቅት ማረፊያ ክፍል እየፈለጉ የሚገኙት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በፌደራል ፖሊስና በደህንነቶች ከፍተኛ ክትትል እየደረሰባቸው መሆኑ ታውቋል፡፡

Tuesday 16 June 2015

ወጣት ሳሙኤል አወቀ ተገደለ


       
የሰማያዊ ፓርቲ የምስራቅ ጎጃም ዞን ፀኃፊና በ2007 ዓ.ም ምርጫ የፓርቲው ዕጩ ተወዳዳሪ የነበረው ወጣት ሳሙኤል አወቀ ተገደለ፡፡ ወጣት ሳሙኤል አወቀ ትናንት ሰኔ 8/2007 ዓ.ም ምሽት ላይ ወደ ቤቱ እየገባ በነበረበት ወቅት በሁለት ግለሰቦች ከፍተኛ ድብዳባ ከተፈፀመበት በኋላ ሆስፒታል ውስጥ ነፍሱ አልፋለች፡፡
ወጣት ሳሙኤል ከቀድሞው አንድነት ጀምሮ ሲታገል የቆየ ሲሆን የሰማያዊ ፓርቲ መስራች አባል ነው፡፡ በአካባቢው የሚፈፀሙ በደሎችን ለሚዲያ በማጋለጥ ሲያበርክተው ከነበረው ሚና ባሻገር በፓርቲው በነበረው ጠንካራ እንቅስቃሴ ምክንያት በተደጋጋሚ እስርና ድብደባ ተፈፅሞበታል፡፡
I am shocked to hear of the death of our leader Samuel Awoke, a brilliant young man, visionary leader and human dignity defender. His young precious life was cut too soon last night by soulless and immoral thugs of the TPLF/EPRDF.
Our brother Samuel is not just some unknown Ethiopian; he is one of us. He is the son, brother, uncle, best friend, valued colleague and extraordinary leader of all of us. Ethiopia has lost an amazing leader and freedom fighter.
I am sure his absence in this world of gun and greed will be deeply grieved by all of them and our thoughts and prayers are with them at this time. He is part of our greater Ethiopian family and together, we mourn the loss of his life. He is one of the many Ethiopians who has been deprived of his life.
Our beautiful country is in darkness today because we have lost that spectacular, gentle and harmless light of Debre Marqos that comes pouring through giving us hope to say YES IT CAN BE DONE. Ethiopia will be free from ethnic hatred politics and ethnic aparthied policy.
May Samuel Awoke’s family and loved ones find comfort, hope and inner strength in this time of great pain and difficulty

Saturday 13 June 2015

የሱዳን ጦር የኢትዮጵያ ድንበር በመጣስ ጥቃት ፈጸመ

ኢሳት ዜና (ሰኔ 4 2007)
የሱዳን መከላከያ ሰራዊት የኢትዮጵያ ድንበር በመጣስ በጎንደር አብደራፊ አካባቢ በባለሃብቶች ይዞታ ላይ ጥቃት መፈጸሙን እማኞች ለኢሳት ገልጹ። ከቀናት በፊት ወታደሮች በባለሃብቶች የእርሻ ተቋማት ላይ በፈጸሙት ጥቃት ተሽከርካሪዎችና ግምቱ ከፍተኛ የሆነ ንብረት በእሳት ቃጠሎ ውድመት እንደደረሰበት ታውቋል።
ከ 20 እስከ 30 ኪሎሜትር የሚሆን የኢትዮጵያ ድንበር ጥሰው የገቡ የሱዳን ወታደሮች የፈጸሙት ድርጊት ምክንያት እንዳልታወቀና እርምጃው በአካባቢው ነዋሪ ዘንድ ስጋት ፈጥሮ መገኘቱን እማኞች ከኢሳት ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ አስረድተዋል። ለጊዜው በሰዎች ላይ ስለደረስ ጉዳት የታወቀ ነገር አለመኖሩን የገለጹት ነዋሪዎች፥ ለወታደሮች ጥቃት ከኢትዮጵያ ወገን የተሰጠ ምላሽ አለመኖሩን አስታውቀዋል።
የሱዳን ወታደሮች እና ታጣቂዎች ተመሳሳይ ድርጊትን ከዚህ በፊት ሲፈጽሙ እንደቆዩ የገለጹት እማኞች፥ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በቅርብ ርቀት ቢገኝም ምንም አይነት አጸፋ አለመውሰዱ በነዋሪዎች ዘንድ ቅሬታ ማሳደሩም ታውቋል። በሁለቱ ሃገራት መካከል ተፈጽሟል የተባለውን ድንበር የማካለል ስምምነት ተከትሎ የሱዳን የጸጥታ ሀይሎች በአካባቢው ተመሳሳይ ጥቃት ሲፈጽሙ መቆየታቸው የሚታወስ ነው።
ከዚህ በፊት አብደራፊ በተፈጸመ ተመሳሳይ ድርጊት በአካባቢው ሰፍሮ የሚገኘው የመንግስት የፀጥታ ሃይል የአካባቢው ነዋሪ ምንም አይነት እርምጃ እንዳይወስድ ሲያሳስቡ መቆየታቸውን ከእማኞች ለመረዳት ተችሏል። በሰሞን (ቅዳሜ) ድንበር በመጣስ በሱዳን ወታደሮች ተወስዷል ስለተባለው ወታደራዊ እርምጃ ከኢትዮጵያ ወገን የተሰጠ ምላሽ የለም።
የኢትዮጵያ ባለስልጣናት በሁለቱ ሀገራት ተፈጽሟል የተባለውን የድንበር ስምምነት ተከትሎ ምንም አይነት መሬት ለሱዳን እንዳልተሰጠ ሲያስተባብሉ መቆየታቸው ይታወቃል። የተፈጸመውም ስምምነት ከዚህ በፊት የነበሩ መንግስታት የፈጸሙት ውል ነው ሲሉ ባለስልጣናት ገልጸዋል።
ሁለቱ ሃገሮች የፈጸሙት የድንበር ስምምነት በርካታ ለም መሬትን ለሱዳን የሚሰጥ ነው በማለት የኢትዮጵያ ድንበር ኮሚቴን ጨምሮ የተለያዩ ኢትዮጵያውያን ድርጊቱን ሲቃወሙ መቆየታቸውም የሚታወስ ነው።
በአብደራፊ ተፈጽሟል የተባለውን ጥቃት አስመልክቶም የሱዳን መንግስት የሰጠው ምላሽ የለም።
ምንጭ፤-ኢሳት

Friday 12 June 2015

በዛሬው ኢሳት ሬዲዮ ስርጭት

በዛሬው ኢሳት ሬዲዮ ስርጭት
-ከኤርትራ በረሃ፤ ከኢትዮጵያ የነጻነት ታጋዮች የጦር ካምፕ ሰራዊቱ ለኢትዮጵያ ህዝብ መልእክት አስተላልፏል። በስልጣን ላይ ያለውን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ የሚመራውን መንግስት ለማስወገድ ኢትዮጵያውያን ትግሉን እንዲቀላቀሉ ሰራዊቱ ጥሪ አድርጓል።
-የሱዳን የመከላከያ ሰራዊት ድንበር ጥሶ፤ ወሰን አልፎ፤ ከኢትዮጵያ አፈር፤ ከኢትትዮጵያ ምድር ላይ ሰፍሮ ኢትዮጵያውያንን ማጥቃቱን አጠናክሮ ቀጥሏል። ባለፈው ቅዳሜ በአብደራፊ አከባቢ የሱዳን ወታደሮች በሁለት ኢትዮጵያውያን ባለሀብቶች ይዞታ ላይ ጥቃት ፈጽመው አውድመውታል። ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ የሚመራው ሰራዊት ለሱዳን ወታደሮች ፍቃድ ሰጥቶ ጥቃቱን እንዲፈጽሙ እንዳደረገ ተገልጿል። ኢትዮጵያውያንን የህወሀት ሰራዊት ማስደብደቡን የኢሳት ምንጮች ከላኩት መረጃ ለማወቅ ተችሏል።
-የቴፒው ትንቅንቅ አሁንም ቀጥሏል። ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ የቴፒ ወጣቶች ቡድን በአንድ ፖሊስ ጣቢያ ላይ በወሰደው ድንገተኛ ጥቃት 3ፖሊሶችን ከገደለና በርካታ እስረኞች እንዲያመልጡ ካደረገ በኋላ የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ሰራዊት አከባቢውን በመክበብ ጥቃት መፈጸም ጀምሯል። የወጣቶቹ ቡድን መሽጎበታል በሚል ውጊያ የጀመረው የህወሀት ሰራዊት ጠንከር ያለ የአጸፋ ምላሽ እንደገጠመው ለኢሣት የደረሰው መረጃ ያመለክታል። በውጊያው በርከት ያሉ የህወሀት ሰራዊት ወታደሮች ሙትና ቁስለኛ መሆናቸውም ታውቋል። የህወሀት ልሳን የሆነ ሬዲዮ ፋና እስር ቤት ሰብረው እስረኞችን ያስመለጡ ሽፍቶች ተገደሉ ሲል ዘግቧል።
- ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ የሚመራው መንግስት በሀገሪቱ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ማፈኑን ተከትሎ የተቃዋሚ ፓርቲዎች "ቅድሚያ ነጻነት" ወደሚል ትግል ማዘንበላቸውን የእንግሊዙ ዘ-ጋርዲያን ጋዜጣ ዛሬ ዘገበ። አፈናው በመባባሱ ተቃዋሚዎች ሌሎች አማራጮችን እንዲመለከቱ እያስገደዳቸው እንደሆነ ጋዜጣው አስነብቧል።
http://ethsat.com/?p=33289

Thursday 4 June 2015

The real terrorists of 2015 are no....

Ethnic apartheid regime of the TPLF/EPRDF has often garnered more support from the West whenever they can claim they are fighting “terrorists.” TPLF/EPRDF regime also use these false flag tactics for propaganda that justifies maintaining a tight grip on the country lest it become a failed state like Somalia.
The whole country is now considered potential or actual terrorists as the regime’s fear of its own people has reached unprecedented levels. To stay in power, they are terrorizing the entire country so now, no one trusts each other, even in families, as spies are everywhere and they are the ones who obtain the perks—the jobs, the education, the business opportunities, food aid or seeds for their crops. The only difference between the TPLF of the past and the TPLF/EPRDF of today is that the terrorism is state-sponsored.
The regime targets anyone any who resists them even if that resistance is in the form of a critical but truthful media report. The real terrorists of 2015 are no longer called guerrilla fighters or rebels, they have titles like prime minister, minister of foreign affairs, minister of agriculture, or governor; however, those who expose them can now be charged as terrorists under this new anti-terrorism law that basically criminalizes truth.