Monday 28 March 2016

ሕወሓት ካድሬዎቿን ይዛ ወደ አፋር ክልል ለመስፋፋት #ሽኸት_ናብ_ትግራይ_ትመለስ ዘመቻ ጀምራለች::

ሕዝብ ለሕዝብ የሚያናክሰው የሕወሓት የመስፋፋት ፖሊሲ ተከዜን የወልቃይት እና ጠገዴን ምድር ከነሕዝቡ ወደ ትግራይ በማካለል በአከባቢው ከፍተኛ የፖለቲካ ቀውስ እንዲነሳ ያደረገ ሲሆን ቀውሱ እየተባባሰ ሕዝቡ መሳሪያውን እንደታጠቀ በዱር ሲገኝ በሽምግልና ለማዘናጋት እና ጊዜ ለመግዛት ሽምግልና አልቀመጥም ሲሉ በግዳጅ በዛቻ የሽምግልናው መሪ የሆኑት አንድ ጳጳስ ጨምሮ የተደረገው ሙከራ እንደተንጠለጠለ ይገኛል::#ሽኸት_ናብ_ትግራይ_ትመለስ የሚለው ዘመቻ የአፋር ክልል ወረዳዎችን በሙሉ ከጥንት ጀምሮ የትግራይ መሬዎች ናቸው የሚል እደምታ ይዞ ተጀምሯል::

እንዲሁም በቅማንት ሕዝብ አከባቢ እየተደረገ ያለው ሕዝብን የማጨፋጨፍ እና የመጨፍጨፍ ስራ በተክል ድንጋይ እንዲፈነዳ የተደረገ ሲሆን የውልቃይት ሕዝብን ጥያቄ ለማድበስበስ እና ለጊዜ መግዣ የሚደረጉ ሕወሓታዊ ተኮሎች ቀጥለዋል::አስተዳደራዊ ጉዳዩን መቀሌ እየመጣ እንዲያስፈጽም እየተደረገ ያለው የቅማንት ሕዝብን ወደ ትግራይ ጠቅልሎ እስከ ጎንደር መግቢያ ድረስ ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት እስካሁን ሊሳካ አልቻልም::ለዚህ ስራ የሚረዱ የሕወሓት ሚሊሻዎች እና የጦር መሳሪያዎች ካለፈው ሳምንት ጀምሮ እየተንጠባጠቡ በአከባቢው ሰፍረዋል::ሕዝቡን ይህንን በማወቁ መሳሪያውን ወልውሎ በተግባር እየተንቀስቀሰ ለሕወሓት ጦር የእግር እሳት ሆኖበታል::

ይህንን የአማራ ክልልን ሰነጣጥቆ የራሱን ግዛት ለማስፋፋት የሚመኘው የሕወሓት አገዛዝ የሱዳን ድንበርን ይዞ ከኩምሩክ ጀምሮ እስከ ሁመራ ድረስ የጉምዝ ተወላጆችን እና የሕወሓት ሚሊሻዎችን በማስፈር አስፈላጊውን እየሰራ ሲገኝ በአፋር ክልል ደግሞ ለመስፋፋት ያለውን እቅድ ለማሳካት #ሽኸት_ናብ_ትግራይ_ትመለስ የሚል አዲስ ዘመቻ በካድሬዎቹ እና በአሽቃባጭ ዘረኛ አማሳኞቹ በኩል ዘመቻ መጀመሩን ታውቋል::ይሕው ዘመቻ ተያይዞ የአፋር ክልል ሕዝብን አሳዶ ግዛቱን በማስፋፋት አከባቢዎቹን ከትግራይ ክልል ጋር ለመቀላቀል ነው::ይህ #ሽኸት የተባለ ቦታ ከጥንት ጀምሮ የትግራይ መሬት ነው ለስራ ጉዳይ አፋር ክልል የገቡ መሬትች ስለሚገኙ ከትግራይ ካልተቀላቀለ በትግሪኛ ትምሕርት ካልተሰጠ አፋርና አከባቢው ላይ መነገር ካልቆመ ለትግራይ ትልቅ ችግር አለ በማለት ሕወሓት እና ካድሬዎቹ እያራገቡ ነው::

መቀሌ ላይ ከሀሙስ ጀምሮ እስከ ትላንት ድረስ የተካሄደው ሚስጢራዊ ስብሰባ ምን ይሆን?

መቀሌ ላይ ከሀሙስ ጀምሮ እስከ ትላንት ድረስ የተካሄደው ሚስጢራዊ ስብሰባ ምን ይሆን? ሾልከው የሚወጡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ህወሀቶች የወልቃይቱንና የድንበሩን ጉዳዮች በቅማንት የማንነት ጥያቄ ለመቀልበስ እየመከሩ ነው። በዚህ ሚስጢራዊ ስብሰባ ከመቀሌ ዩኒቨርሲቲ ጨምሮ ከተለያዩ ቦታዎች የተጋበዙ የትግራይ ምሁራን ተገኝተዋል። ወጣቶችም ተሳትፈዋል። አባይ ወልዱና ቁልፍ የህወሀት የደህንነትና ወታደራዊ ሰዎች ነበሩ። በአማራ የተጀመረው ንቅናቄ በደንብ እግር አውጥቶ ከመራመዱ በፊት መስበር ስለሚቻልበት ሁኔታ ሲመክሩበት ነበር። ለአሁን የቅማንትን የማንነት ጥያቄ ወደለየለት የእርስ በእርስ ግጭት መቀየር የሚለው ሀሳብ ተቀባይነት አግኝቷል።

Sunday 27 March 2016

የሕወሓት የመስፋፋት እቅድ የወለደው የእርስ በእርስ ጦርነት በተክል ድንጋይ ፈንድቷል::

Mereja
ከትላንትና ጠዋት ጀምሮ የሚደርሱ መረጃዎችን ተከትሎ ለማረጋገጥ እንደተቻለው የሕወሓት የመስፋፋት ፖሊሲ እና ታላቋን ትግራይ የመመስረት አላማውን ለማሳካት ሲል የሚሰራቸው እኩይ ተግባራት በሰሜን ኢትዮጵያ የተፈራው የእርስ በእርስ ጦርነት በጎንደር ክፍለሃገር ተክል ድንጋይ መፈንዳቱን ከአከባቢው የተገኙ መረጃዎች ጠቁመዋል::ሕወሓት የቅማንት ሕዝብን ለእኩይ ተግባሩ ሊጠቀምበት በማሰብ ከፍተና የሆነ የጦር መሳሪያ እያስገባ ነው የሚሉ የተክል ድንጋይ ነዋሪዎች ይናገራሉ::በአምቡላስ ላይ የደረሰን የፈንጂ አደጋ ተከትሎ ከትላንትና ጀምሮ በሕወሓት የጦር ሰራዊት እና በጎንደር ክፍለሃገር ሕዝብ መካከል ግጭቶች ወደ ተኩስ በመለወጣቸው አከባቢውን የጦር አውድማ አድርገውታል::

በትላንትናው እለት በትክል ድንጋይ በአምቡላንስ ላይ የፈንጂ ጥቃት ደርሶ በአምቡላንሱ ውስጥ የነበሩ ሁለት ሲገደሉ በአንዱ ላይ የመቁሰል አደጋ ደርሶ የነበረ ሲሆን የአከባቢው ሕዝብ ለአደጋው የሕወሓትን ሰራዊት ተጠያቂ አድርጓል::እንዲሁም ሁለት ታዳጊ ወጣቶች በሕወሓት ጦር መገደላቸውን የአከባቢው ነዋሪዎች ይናገራሉ::ወደ ተክል ድንጋይ የሚያስገቡ መንገዶች የተዘጉ ሲሆን የሕወሓት ጦር በአከባቢው ውጥረት በመፈጠሩ መሳሪያ ያልታጠቁ ነዋሪዎች ራሳቸውን ከሕወሓት ጦር ለማዳን ወደ ጎረበት ወረዳዎች እየሸሹ ይገኛሉ::መሳሪያ የታጠቁ የተክል ድንጋይ ነዋሪዎች ከወያኔ ጦር ጋር እየተታኮሱ ይገኛሉ:: 

7 የሕወሓት ባለ ስልጣናት ባአማራ ክልል ሌላ ሴራ ጠንስሰዋል

ሚስጢራዊ መረጃ
የማስጠንቀቃያ ደውል ለአማራ ኢትዮጵያ በሙሉ
============%================
7 የሕወሓት ባለ ስልጣናት ባአማራ ክልል ሌላ ሴራ ጠንስሰዋል ፡፡
==> ወልቃይት ዳንሻ ላይ የተለኮሰውን የማንነት ጥያቄ ለማቀዝቀዝ ሌላ መንገድ ቀይሰዋል ፡፡
==> የሕወሓት መሀከላዊ ከሚቴ አባል የሆነው " አቶ ተክለ ወይኒ አሰፍ እና አስፋው ምሀሪ በሚባል የደህንነት አባል የሚመራ የኦሮ በላ ቡድን ተቋቁሟል ፡፡
==> ለነዚህ ኦሮ በሎች የተሰጣቸው ተልዕኮ የሚከተለው ነው ፡፡
1 ኛ አማራ ክልል ላይ ያሉ የተራድኦ ድርጅቶችን መዝረፍ ፡፡
2 ኛ ከሁመራ ሰሊጥ እና ቦሎቄ የጫኑ መኪኖችን መዝረፍ፡፡
3ኛ ቤተ ክርስቲያን እና የህዝብ መገልገያዎችን መዝረፍ እና ማውደም ፡፡
4 ኛ የአማራ ተወላጅ ሁነው  በመንግሥት ሥራ የተሰማሩ
ነገር ግን ስራቱን የማይደግፉትን " በሥራቸው ምክንያት ህዝብ የገደላቸው በማስመሰል መግደል ይላል የተሰጣቸው ተልዕኮ ፡፡ ባጠቃላይ አማራ ክልል ላይ ትልቅ ቀውስ መፍጠርን አላማ አድርጓል ፡፡
=> እነዚህ ችግሮች በመፍጠር የህዝቡን ስሜት በመክፈል ለጊዜውም ቢሆን ወልቃይት እና ዳንሻ ላይ ያለውን አመጽ ለማቀዝቀዝ ነው ፡፡
=> ከዚህም ጉንለጎን ወልቃይት እና አጎራባች አካባቢ ያለውን የህዝብ ንብረት ወደ መቀሌ ለማጓጓዝ ጊዜ ለማግኘት መሆኑ ታውቋል ፡፡
==> ስለዚህ ሁሉም የአማራ ህዝብ በያለበት በተጠንቀቅ ሊቆም ይገባል ፡፡ የዚህ አይነት ችግር ሲፈጥሩ የተገኙ ወዲያውኑ እርምጃ ይወሰድባቸው !!! አማራም ይሁኑ ትግሬ ወይም የሊላ ብሔር ፡፡
=> ማንም ይሁን የተወጣለትን አላማ ወደ ጉን ትቶ በዚህ ስራ ከተገኘ ወዲያውኑ እርምጃ ሊወሰድበት ይገባል ፡፡
=> ምክንያቱም የአማራ ወጣቶች እና የህዝቡ ፋላጉት ንብረት ማውደም እና መዝረፍ አይደለም ፡፡ የማንነት ጉዳይ እንጂ ፡፡

Friday 25 March 2016

የተደበቀው ረሀብ

የሀገር ገጽታ እንዳያበላሽ"ተብሎ የተደበቀው  የረሀብ ጉዳት እየተጋለጠ ነው። በሶማሌና አፋር ክልሎች ህጻናት ሥጋቸውና አጥንታቸው ተጣብቆ የሞት ሲቃ እያቃሰቱ ነው። ፎቶውን የላኩት የረድ ኤት ሠራተኛ ሁኔታው ራስህን እንድትጠላ ያደርግሀል" ይላሉ።

Tuesday 22 March 2016

አንድን ሕዝብ ጠላቴ ብሎ የፈረጀ መንግሥት አገዛዝ የወደቀ ሕዝብ ነው የሰሜን ጎንደር ሕዝብ ።

ኧረ ወገን መላ ፈልጉ ለወልቃይት ጠገዴና ታች አርማጭሆ ሕዝብ ።
     አንድን ሕዝብ ጠላቴ ብሎ የፈረጀ  መንግሥት አገዛዝ የወደቀ ሕዝብ ነው የሰሜን ጎንደር ሕዝብ ።
   በጎንደር የምትገደለው የምታታሰረው የምትታፈነው ጥፋተኛ ወይም አልገዛም ወይም የመብት ጥያቄ አንስተህ አይደለም ።
  በመጀመሪያ አስተሳሰብህ በአካባቢው ሰው ያለህ ተቀባይነት ነው ።
     በ21ኛው ክ/ ዘመን ይደረጋል ተብሎ የማይጠበቅ እየተደረገ ነው ።
    ወገን መላ ፈልጉ አሁንም ቀኑ አልመሸም አንድ መላ ፈልጉ ።
በትግራይ መስተዳድር  የጎንደር ሕዝብ እየተጠቃ ነው ።
  አባይ ወልዱ የሕውሓት መሪ በመለስ ዜናዊ ወንበር የተቀመጠ ዘመናዊ የ21ኛው ክ/ ዘመን  ሂትለር ነው ።
የማንኛውም  በየቀኑ የሚገደሉት አማራዎች በዚህ ፋሽሽት ትዕዛዝ ነው ።የኢትዮጵያ መሬት ለሱዳን የሚሰጠውም በዚህ ግከሰብ ትዕዛዝ ነው ።
ይህ ግለሰብ ከአዲስ አበባው መንግሥት ይልቅ ካርቱም ያለው ይቀርበዋል ።
ከሁመራ ሲመክር ሲዶልት ውሎ አዳሩ ገዳሪፍ ነው ።
አባይ ወልዱ ከትግራይ ይልቅ በሱዳን ተዝናንቶ  የሚሄድበት አገሩ ነው ።
   ምንም ጥርጥር የለሌለው ፀረ አማራ በፀረ አማራነቱ ተለክቶ ነው የሕውሓት መሪ የሆነው ።
በሕውሓት ዘንድ ወደከፍተኛ ስልጣን ለመድረስ መለኪያ የዘረኝተህ ደረጃ ታይቶ ነው ።
    ደብረ ፅዮን የተባለውም የትምህርት ደረጃው ታይቶ አይደለም የሥውሩ መንግሥትን እየመራ ያለው ።
  ያው ታዋቂ ኢትዮጵያውያን ላይ በሚያቀናብረው ስልታዊ ተንኮሉ ነው።
   በፕሮፊሰር አስረሰት ላይ  የሀሰት ውንጀላውን ያዘጋጀው እሱ ብቻ እንደነበረም  አብሮት ይሰራ የነበረ ያጋለጠው ቪዲዮ በእጃችን ላይ ይገኛል ። shagi

Monday 21 March 2016

የወልቃይት ህዝብና የትግራይ ልዩ ኃይሎች በመዋጋት ላይ ናቸው፡፡

(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ)
ትግራይና ወልቃይትን የሚያገናኙ ጎዳናዎች መዘጋታቸው ተነገረ፤ ፌደራል ፖሊስና የትግራይ ልዩ ኃይል የወልቃይትን ምድር ወሮታል፡፡
የወልቃይት ህዝብ ያነሳውን የአማራ ማንነት ጥያቄ ለመቀልበስ ህወሓት አጠናክሮ የጀመረውን በህብረተሰቡ ዘንድ ተቅባይነት ያላቸውን ግለሰቦች አፍኖ ድብዛቸውን የማጥፋት ተግባር በመቃወም የወልቃይት ህዝብ እርምጃ መውሰድ ጀምሯል፡፡ በመሆኑም ዋና፣ ዋና መንገዶችን በጠብመንጃ አጥሮ በመዝጋት ተከዜን ተሻግሮ ከትግራይ ወደ ወልቃይት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን በመግታት ላይ ነው፡፡
የወልቃይት ታጣቂ ኃይሎች ከወለቃይትና ትግራይ ወሰን ላይ በመመሸግ በእግርም ወደ ወልቃይት የሚጓዙ ሰዎችን መታወቂያ መጠየቅ ጀምረዋል፡፡
በአዲ ጎሹ በኩል ከትግራይ ወደ ወልቃይት የሚያስገባው አውራ ጎዳና እና እንዲሁም በተጨማሪ ከሁመራ ወደ ጎንደር የሚሄደው መንገድ በወልቃይት ታጣቂ ኃይሎች ቁጥጥር ስር ውለው ተዘግተዋል፡፡
ትናንትና ጠዋት ከወደ ትግራይ የተነሳች መኪና “ካዛ” ላይ መሽገው በነበሩት የወልቃይት ታጣቂዎች ተኩስ ተከፍቶባታል፡፡
ህወሓት ከትናንት ወዲያ አፍኖ የወሰዳቸው የወልቃይት የአማራ ማንነት ጥያቄ አስተባባሪ ኮሚቴ አባል የሆኑት “አቶ ሊላይ ብርሃነ” ደብዛ መጥፋትና “ሩዋልሚ” ከተባለ ወንዝ ዳር አንድ ማንነቱ ሊለይ ያልቻለ አስከሬን መገኘቱ የህዝቡን ቁጣ እንዳባባሰው ተገልጿል፡፡
እናም ህወሓት ከፍተኛ ቁጥር ያለው ፌደራል ፖሊስና የትግራይ ክልል ልዩ ኃይል ጦር በወልቃይት ምድር አሰራጭቶ በተለይም ደግሞ ዳንሻ በሰራዊት ተከባ ትገኛለች፡፡ የወልቃይት ህዝብና የትግራይ ልዩ ኃይሎች በመዋጋት ላይ ናቸው፡፡

Saturday 19 March 2016

ከግንቦት 7 መሰራቾች አንዱ እና ዋና ጸሃፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሁኔታ ያሰጋቸው የታላቋ ብሪታኒያ ጠ/ሚ/ር ዲቪድ ካሜሮን ለኢትዮጵያው አቻቸው ለአቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ለሁለተኛ ጊዘ ደብዳቤ መጻፋቸውን ( ቡዝ ፌድ ነውስ) የተባለው ድህረገጽ ከእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ መ/ቤት ያገኘውን መረጃ ትነተርሰሶ በተላንተናው እለት( ሃሙስ መጋቤት 17 2016) እትሙ ዘግቧል።

ላለፉት ሁለት አመታት ያህል በእስር ላይ እየማቀቁ እንደሚገኙ የሚታመነው ከግንቦት 7 መሰራቾች አንዱ እና ዋና ጸሃፊ የሆኑት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሁኔታ ያሰጋቸው የታላቋ ብሪታኒያ ጠ/ሚ/ር ዲቪድ ካሜሮን ለኢትዮጵያው አቻቸው ለአቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ ለሁለተኛ ጊዘ ደብዳቤ መጻፋቸውን ( ቡዝ ፌድ ነውስ) የተባለው ድህረገጽ ከእንግሊዝ የውጪ ጉዳይ መ/ቤት ያገኘውን መረጃ ትነተርሰሶ በተላንተናው እለት( ሃሙስ መጋቤት 17 2016) እትሙ ዘግቧል።አንደ ዜና ዘገባው እምነት ከሆነ ምንም እንኳን የደብዳቤው ይዘት እና መቺ እንደተጻፈ ባይጠቀስም “ከሎንዶን ደጎስ ያለ የእርዳታ ገንዘብ (በአመት 350 ሚሊዮን የእንግሊዝ ፓውንድ) የሚፈሰላት አዲስ አበባ ከወዳጅ አገር ለቀረበላት (አንዳርጋቸው ባስቸኳይ ይፈቱ ጥያቄ) ብዙም ፈቀቅ ያለ እንቅሰቃሴ (አውንታዊ ምላሽ)አላሳየችም” ተብሏል። ከዚህ አኳያ የእንግሊዝ ዜግነት ያላቸው፡ የሰሜናዊ ሎንዶን ነዋሪ የነበሩት፡ የሶስት ልጆች አባት እና ባለትዳሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን ሰነእ ላይ ታግተው ወደ አትዮጵያው ማጎርያ ቤት ከተወረውሩ ጀምሮ ለተደጋጋሚ ጊዜያት ደብዳቤዎችን ቢላላኩም ባለው ሁኔታ ላይ ለውጥ በለመገኘቱ የአንግሊዝ ባለሰላጣናት በእጅጉ መበሳጨታቸውን ዘገባው የወጪ ጉዳይ ባለሰልጣናትን ጠቅሶ አሰፍሯል።

Wednesday 9 March 2016

የሕወሓት ካድሬዎች በኮንዶሚኒየም ቤቶች ላይ የሚያደርጉት ሕገወጥ ተግባር በቆጠራ ተደረሰበት::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ባለፉት አሥር ዓመታት የገነባቸውን የ20/80 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ያሉበትን ደረጃ ለማወቅ በጀመረው ቆጠራ፣ በሕወሓት ካድሬዎች  በርካታ ሕገወጥ ተግባራት የተፈጸሙባቸው ቤቶች መኖራቸው ታወቀ፡፡

የካቲት 21 ቀን 2008 ዓ.ም. የተጀመረው ቆጠራ ሳምንቱን የያዘ ሲሆን፣ ይቆጠራሉ ከተባሉት 104,258 ቤቶች ውስጥ 35 ሺሕ ያህሉ ተቆጥረዋል፡፡ በዚህ መሠረት በሕወሓት ካድሬዎች   ተሰብረው የተከራዩ፣ ፈርሰው ተቀላቅለው የተሠሩ፣ በግለሰቦች የተያዙ በርካታ ቤቶች መኖራቸው ተረጋግጧል፡፡ በተጨማሪም ትዳር እየፈረሰና ፍቺ እየተፈጸመ መሆኑን መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ በትዳር ውስጥ እየኖሩ ነገር ግን ከሁለት በላይ ቤቶች ይዘው የተገኙ ፍቺ እስከመፈጸም የደረሱ ክስተቶች መገኘታቸውን ከአዲስ አበባ ቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ የተገኙ መረጃዎች አመልክተዋል፡፡ ከዚህ በላይ ተገቢው ክፍያ ያልተፈጸመባቸው ቤቶችን መያዝና ሕጋዊ መረጃ የሌላቸው ቤቶችም መገኘታቸው ተመልክቷል፡፡
ለባንክ ተገቢውን ክፍያ በወቅቱ ያልፈጸሙ፣ በሕገወጥ ድርጊት ከያዙት ቤት የኮበለሉና በሕገወጥ ድርጊታቸው በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉ መኖራቸውም ታውቋል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በዘጠኝ ዙሮች ለተጠቃሚዎች ያስተላለፈውን 104,258 ቤቶች ቆጠራ ጀምሯል፡፡ ባለፈው ሳምንት የተጀመረው ቆጠራ ብዙ ቤቶች በተገነቡባቸው ንፋስ ስልክ ላፍቶ፣ ቦሌ፣ የካ፣ አቃቂና ኮልፌ ቀራኒዮ ክፍላተ ከተሞች ነው፡፡
በቆጠራው 2,500 ባለሙያዎች፣ ፖሊስ፣ ደንብ ማስከበርና የንግድ ቢሮ ተሳታፊዎች ሆነዋል፡፡
ቆጠራውን በሚመለከት የአዲስ አበባ ቤቶችና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ይድነቃቸው ዋለልኝና የአዲስ አበባ ቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ ኃላፊ አቶ መስፍን መንግሥቴ መግለጫ በሰጡበት ወቅት፣ አስተዳደሩ በእነዚህ ቤቶች ሕገወጥ ተግባራት እየተፈጸመ መሆኑን የሚገልጽ ሪፖርት እንደደረሰው ገልጸው ነበር፡፡
አስተዳደሩ ለልማት ተነሺዎች 8,400 ባለአንድ ክፍልና ስቱዲዮ ቤቶችን አዘጋጅቶ ነበር፡፡ ነገር ግን የልማት ተነሺዎች ፍላጐት ባለሁለት ክፍልና ባለሦስት ክፍል በመሆኑ፣ በርካታ ቤቶች ጥቅም ላይ ሳይውሉ ተዘግተው ቆይተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ለተጠቃሚዎች ቢቀርቡም ውል ስላልተፈጸመባቸው ርክክብ ያልተፈጸመባቸው 4,137 ቤቶች ይገኛሉ፡፡ በዚህ ሒደት በሕወሓት ካድሬዎች  ደላሎች፣ የጥበቃ ሠራተኞችና ሌሎች አካላት አብዛኛዎቹን ቤቶች በመስበርና በመቀላቀል ለግል ጥቅም ማዋላቸው ተነግሯል፡፡
ቆጠራው ትኩረት የሚያደርገው መኖሪያ ቤቶች፣ ንግድ ቤቶችና የጋራ መጠቀሚያዎች ላይ ነው፡፡ በእነዚህ ግንባታዎች ላይ ሕገወጥ ድርጊት ተፈጽሞ ከተገኘ፣ ሕግ የማስከበር ሥራ እንደሚሠራ አቶ መስፍን በወቅቱ ተናግረዋል፡፡
ከዚህ ቆጠራ የሚጠበቀው ከተጠቃሚዎች የሚገኘው መረጃ ከአስተዳደሩ መረጃ ጋር ተመሳክሮ ዕርምጃ እንደሚወስድ ነው፡፡ ቆጠራው ከዚህ በተጨማሪ ለወደፊቱ ተመሳሳይ ችግር እንዳይከሰት ማስተካከያ ማድረግ እንደሚያስችል  ይድነቃቸው ተናግረዋል፡፡
እስካሁን በተደረገው ቆጠራ 42 በመቶ ቤቶች እንደተሸፈኑ፣ 1,339 ቤቶች ባዶ ሆነው መገኘታቸውንና በሕገወጥ ሥራ ተሰማርተው ከተገኙት መሀል 60 ያህሉ በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
Mereja.com