Tuesday 24 May 2016

የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር ዶ/ር ታደሰ ብሩ ከአሜሪካን ሀገር የተለያዩ ሴነተሮችና ባለስልጣናት ጋር በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ።

የአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር ዶ/ር ታደሰ ብሩ ከአሜሪካን ሀገር የተለያዩ ሴነተሮችና ባለስልጣናት ጋር በወቅታዊ የኢትዮጵያ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ።
ዶ/ር ታደሰ ብሩ ለአጭር ጊዜ ጉብኝት አሜሪካን ሀገር የሚገኙ ሲሆን፤ በቆይታቸው ወቅት በኢትዮጵያ የሰባዊ መብት፣ ዴሞክራሲና መልካም አስተዳደር ዙሪያዎች ከአሜሪካን ኮንግረስማን ተወካዮች ጋር ውይይት አድርገዋል። በተለይም ከከሎራዶው ኮንግረስማን ማይክ ኮፍማን ጋር በወቅታዊ እና ዘላቂ መፍትሄዎች ላይ አመርቂ ውይይት ማድረጋቸው ተገልጾል።

ኮንግረስማን ኮፍማን ዶ/ር ታደሰን ስለ ኤርትራ ቆይታቸው ምን እንደሚመስል ጠይቀዋቸው፡- ዶ/ር ታደሰም ሲመልሱ፡- በህወሃት መንግስት የሚደረገው ህዝብን የማጣላት፣ በኢትዮጵያና ኤርትራ ህዝበ መካከል በጠላትነት እንዲተያዩ የሚያደርገው ዘመቻ የተሳሳተ መሆኑን ገልጸው አርበኞች ግንቦት 7 ዘላቂ ወዳጅነትን እየጠናከረ እንደሚገኝ እና የሁለቱ ህዝብ ጠላት TPLF እንጂ ሌላ መሰረታዊ ችግርች እንደሌሉ እና ለኤርትራ ህዝብ ያላቸውን አድንቆት በመግለጽ አብሮ መስራት እንደሚቻል ያላቸውን እምነት ገልጸውላቸዋል። አሜሪካ በኢትዮጵያ የምትከተለውን የውጪ ፖሊሲዋን እንደገና እንድትመረምረውም አሳስበዋል።  አያይዘውም ኮንግረስማን ማይክ ኮፍማንና ሌሎች ሴነተሮች በቅርቡ በሜሪላንዱ ሴነተር ካርደን ቤንጃሚን ተረቆ የቀረበውን Resolution 432 በርካታ ሴነተሮች የፈረሙበትን የኢትዮጵያ ሰበአዊ መብትና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ድጋፋቸውን ይሰጡ ዘንድ ኮንገርሰማኑን ጠይቀዋል።

በመጨረሻም ኮንግረስማን ማይክ ድርጅቱ በሁለቱ ሀገራት ህዝብ መካከል እየፈጠረ ያለውን የሰላም ድልድይ እና የማቀረረብ ሂደት አድንቀው፤ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ጉዳዮችም እንደሚከታተሉ ገልጸውላቸዋል።
Abbay media

ሰበር ዜና.. ጌታቸዉ አሰፋ ስብሰባ አቋር ጦ ወጣ

ሰበር ዜና..
ጌታቸዉ አሰፋ ስብሰባ አቋር ጦ ወጣ..
በትናንትናዉ እለት የወያኔ ተላላኪ ከሆኑት እና ከብሔራዊ መረጃ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ካላቸዉ ግለሰቦች መካከል አምባሳደር ቀጸላ ከብሀራዊ መረጃዉ ሐላፊ ከጌታቸዉ አሰፋ ጋር አርበኞች ግንቦት 7 በአርባ ምንጭ ላይ የወሰደዉን እርምጃ ተንተርሶ ዉይይት በሚያደርጉበት ወቅት በተመሳሳዩ በደቡብ ኢትዮጵያ ኮንሶ አካባቢ በትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት ተፈስሞ ከ 55 በላይ የሚጠጉ የፖለቲካ እስረኞች ማምለጣቸዉ 19 የወያኔ ታጣቂዎች መገደላቸዉና ቁስለኛ መሆናቸዉን የሚያበስር ዜና በስብሰባዉ ላይ የደረሰዉ ጌታቸዉ አሰፋ በአፋጣኝ ስብሰባዉን አቋርጦ መዉጣቱን ታማኝ ምንጮች ገልጸዋል።
አርበኞች ግንቦት 7 በፓርላማ ዉስጥ ሳይቀር መነጋገሪያ እርእስ መሆኑን የገለጹት ምንጮቻችን አክለዉ የወልቃይት ጠገዴ ጉዳይ የፈጠረዉ ፖለቲካዊና ህዝባዊ ጫና እንዳለ ሆኖ በጎንደር አርማጭሆ ሁመራ እና በትግራይ ጎንደር አዋሳኝ በኡማህጅር አካባቢ ድንገተኛና አደገኛ ጥቃቶች መሰንዘራቸዉን እንዲሁም በ24 እና በ25ኛ ክፍለጦር ተዉጣጪ የጸረ ሽብር ሐይል ላይ በተደረገ ሽምቅ ዉጊያ ከፍተኛ ጉዳት መድረሱን መረጃዎች ጠቁመዋል።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !
(ጉድሽ ወያኔ)

Saturday 14 May 2016

በኢትዮጵያ ጥቃት ያደረስኩት እኔ ነኝ ሲል አርበኞች ግንቦት ሰባት ኃላፊነቱን ወስዷል

ሰሞኑን በደቡብ ኢትዮጵያ ጥቃት ያደረስኩት እኔ ነኝ ሲል አርበኞች ግንቦት ሰባት ኃላፊነቱን ወስዷል። የድርጅቱሊቀ መንበር ዶክተር ብርሃኑ ነጋ ዛሬ ከዝግጅት ክፍላችን ጋር ባደረጉት አጭር ቆይታ፥  "ትግላችንን የምናካሂደው እዚያው ኢትዮጵያ ውስጥ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ሆነን ነው" ብለዋል። የኤርትራ መንግሥት አሰልጥኖ የላካቸውን አሸባሪዎች በቁጥጥር ሥር ማዋሉን የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎትና የፌዴራል ፖሊስ ፀረ-ሽብር የጋራ ግብረ ኃይል ማስታወቁ ይታወቃል።

Monday 2 May 2016

በቂሊንጦ እስር ቤት የሚገኘው ወጣት አባይ ዘውዱ ሕይወቱ አዳጋ ላይ መድረሱ ታወቀ፡፡

ከሰሜን ጎንደር ታፍኖ በቂሊንጦ የስቃይ ማጎሪያ የሚገኘው የቀድሞ ኣንድነት ፓርቲ ኣመራር ወጣት ኣባይ ዘውዱ በእስር ቤት ሕይወቱ ሊያልፍ እንደሚችል በከፍተኛ ሰጋት ላይ ወድቋል፡፡ ኣባይ ዘውዱ በደረሰበት የጉበት እና ጣፊያ እብጠት ሊፈነዳ ሲሆን በተጨማሪም በቲቪ-በከፍተኛ ደረጃ መታመሙ በደረሰን ጥቆማ ዛሬ 22/08 ቂሊንጦ በመሄድ ከራሱ ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ወጣት ኣባይ ዘውዱ በህመሙ ሰውነቱ ኣልቆ በሰው ተደግፎ እያቃሰተ ማየት ያማል፡፡  የተሟላ ህክምና እንደተከለከለ ኣባይ እንባውን እያፈሰሰ ይናገራል፡፡ ይህ ለመላው ኣገር ወዳድ በተለይ የኣማራ ሕዝብ በዝምታ ተመልክቶ የወጣት ኣባይ ዘውዱ ሕይወት ልናጣው ከቻልን ለኣማራ ሕዝብ ትልቅ ውድቀት ትልቅ ዋጋ እንደሚያስከፍል መገንዘብ ያሻል፡፡ ኣባይ ዘውዱ-ሁለተኛ ድግሪውን ከቅርብ ጊዜ በፊት ያጠናቀቀ ሲሆን በከፍተኛ ትምህርት የቆይታውም ቢሆን ከባሕር ዳር ዩንቨርስቲ የማዕረግ ተመራቂ የነበረ ወጣት ምሁር ነው፡፡ ኣባይ ዘውዱ የቀድሞ ኣንድነት ፓርቲ ከተቀላቀለ በኃላ በነበረው ንቁ ተሳትፎ ከሚሰራበት ቦታ ከማባረር እንስቶ በኣካሉ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሲደርስበት የቆየ ጠንካራ ጓዳችን መሆኑ ይታወቃል፡፡ በተለይ ለሱዳን ሊሰጥ በታሰበው መሬት ዙሪያ ኣባይ ዘውዱ ከጎንደር ኣዲስ አበባ ድረስ በመምጣት በኣንድነት ፅ/ቤት ሰፊ የዳሰሳ ጥናቱን ካቀረበ ወዲህ በወያኔ አይን እንደገባ ይነገራል፡፡ ለዚህ ጀግና ጓዷችን ኣገር ወዳድ ሊደርስለት ይገባል፡፡ ኣማራ ልጆቹን በዘረኞች እያስበላ የሚኖረው እስከመቼ ነው?
ወጣት አክቲቪስቶች የሚዲያ ኣካሎች በሙሉ ወጣት ኣባይ ዘውዱ የተሻለ ህክምና እንዲሰጠው ግፊት ማድረግ ሕይወቱን መታደግ ግዴታ ኣለበት፡፡ የነቃ ተሳትፎ ያላቸው የኣማራ ተወላጅ የሚደርሰው ዘር የማጥፋት ድርጊት ሊወገዝ ኣምሮ ሊታገሉት የሚገባ ተግባር ነው፡፡ ሁሉም ወገን ወዳድ ለኣባይ ዘዉዱ ድምፁን ያሰማለት፡፡ ኣማራ ነገ ታሪኩ ሲነገር ሊያፍርበት ይችላል፡፡