Wednesday 31 December 2014

ሰበር ዜና

አራት በከፍተኛ ማእረግ ላይ የሚገኙ የአየር ሃይል አብራሪዎች ከድሬዳዋ አየር ሃይል ግቢ በመጥፋት ኬንያ ገቡ
ይህንን ተከትሎ አየር ሃይል ዛሬ ሲታመስ ውሏል።
የደህንነት ሃይሎች የበርካታ አብራሪዎችን ስልኮች ሲፈትሹ ውለዋል። ቁጥራቸው በውል የማይታወቁ አብራሪዎችም ታስረዋል።
ባለፈው ሳምንት 3 አብራሪዎች የሚያበሩትን የጦር ሄሊኮፕተር ይዘው መጥፋታቸው ይታወቃል።
ስለጠፉት አብራሪዎች ተጨማሪ መረጃዎችን እየተከታተልን እናቀርባለን።


Source: ESAT

Ethiopia’s Capital is now Home for prostitute.

Ethiopia’s Capital is now the Home of the Largest Houses of Prostitution in Africa
US State Department.
December 30, 2014
Girls from Ethiopia’s rural areas are exploited in domestic servitude and, less frequently, prostitution within the country, while boys are subjected to forced labor in traditional weaving, herding, guarding, and street vending. The central market in Addis Ababa is home to the largest collection of brothels in Africa, with girls as young as 8-years-old in prostitution in these establishments.
Ethiopian girls are forced into domestic servitude and prostitution outside of Ethiopia, primarily in Djibouti, South Sudan, and in the Middle East. Ethiopian boys are subjected to forced labor in Djibouti as shop assistants, errand boys, domestic workers, thieves, and street beggars. Young people from Ethiopia’s vast rural areas are aggressively recruited with promises of a better life and are likely targeted because of the demand for cheap domestic labor in the Middle East.
የደብረማርቆስ የመሰናዶ ተማሪዎች የመንግስትን ፖሊሲ ተቃወሙ
ተማሪዎች ኢህአዴግን እንዲመርጡ በሚል በግዳጅ በተዘጋጀው የፖለቲካ ስልጠና ላይ ተማሪዎች ፈታኝ የሆኑ ጥያቄዎችን አስተያየቶችን ሰጥተዋል ።
ኢህአዴግ እነ ዶ/ር ብርሃኑ ነጋን የመሰሉ ሰዎችን አሸባሪዎች ማለቱ ትክክል አለመሆኑን የሚገልጹት ተማሪዎች፣ ኢህአዴግን የሚበልጡት በመሉ አሸባሪ እያለ እንደሚፈርጃቸው ተናግረዋል ( )
ፕ/ት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ የሚኖርበት ቤት 400 ሺ ብር እንደሚከፈልበት የተናገሩት ተማሪዎች፣ አባይን መገደብ ያልቻለ መንግስት እንዴት ይህን ያክል ገንዘብ ይከፍላል ሲሉ ጠይቀዋል። ( ) 
በኮምቦልቻ ደግሞ መድረኩን የሚመሩት ባለስልጣን በውጭ አገር የሚገኙ የሚዲያ ተቋማት ትክክለኛ መረጃ አያሰራጩም በማለት መናገራቸውን ተከትሎ ተማሪዎች በውጭ የሚገኙ ሚዲያዎች ከኢቲቪ ቀድመው መረጃ በመናገር ተአማኒነትን ማትረፋቸውን ለዚህም ደግሞ በየጊዜው የሚከዱ ባለስልጣናት አስተዋጽኦ ማድረጋቸውን ገልጸዋል። አቶ በረከት ስምኦን የሂትለር የማስታወቂያ ሚኒስትር የነበረው ጆሴፍ ጎብልስ፣ ውሸት ሲደጋጋም እውነት ይሆናል ያሉትን በተደጋጋሚ እንደሚናገሩና፣ ይህንኑ በኢቲቪ ላይ ተግባራዊ እያደረጉት መሆኑን ተማሪዎች መናገራቸውን መዘገባችን ይታወቃል።
የመለስ ዜናዊን ማረፍ መጀመሪያ የሰማነው ከውጭ ሚዲያዎች ነው፣ ኢቲቪ ዜናውን የነገረን ከ2 ወር በሁዋላ ዘገይቶ በማለት በውጭ ሚዲያዎችን ላይ የቀረበውን ትችት ተከላክለዋል። የመንግስት ባለስልጣናት በየጊዜው መክዳታቸው መረጃ ለማግኘት አስተዋጽኦ ማድረጉን የገለጹት ተማሪዎች፣ ኢሳት በጋዜጠኛ አበበ ቶላ ወይም አቤ ቶክቻው አማካኝነት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጋዜጠኞችን ህብረት ፕሬዚዳንትን ቃለ ምልልስ በማድረግ ያቀረበው ዘገባ፣ የመንግስት ባለስልጣናት እውነተኛ ፍላጎት የሚያሳይ ነው ሲሉ አክለዋል። ( )
በጋምቤላ በመዠንገር አካባቢ የደረሱ ጭፍጨፋዎችንና ሌሎችንም በርካታ የአገራችን ችግሮች የሰማነው በውጭ ሚዲያው በመሆኑ፣ በሚዲያው ላይ የሚቀርበው ወቀሳ ትክክል አይደለም ብለዋል።
የብሄር ግጭትን በተመለከተ ዋናው ተጠያቂው መንግስት ነው ያሉት ተማሪዎች፣ በተለይ የትግራይን ህዝብ ከአማራውና ከኦሮሞው ጋር ለማጋጨት የሚያደርገው እንቅስቃሴ በሁዋላ ላይ አገሪቱን ይጎዳታል ሲሉ አስጠንቅቀዋል።
ተማሪዎች ካነሱዋቸው ቅሬታዎች መካከል አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ በስልጤ ወራቢ ተገኝተው ስለተናገሩት እና በቀይ ባህር ላይ ስላለቁት ኢትዮጵያውያን ይገኝበታል። አንድ ጠ/ሚኒስትር እንዴት የገዛ ዜጎችን ገረድ ብሎ ይሳደባል ሲሉ የጠየቁት ተማሪዎች፣ እንዲህ አይነት ንግግር እንኳንስ አገር ከሚመራ ከተራ ዜጋም አይጠበቅም በማለት ተችተዋል። መንግስት ለመለስ ዜናዊ ከፍተኛ ገንዘብ በማውጣት በስርአት እንዲቀበሩ ማድረጉን ያስታወሱት ተማሪዎች፣ በቅርቡ ወደ የመን ሲሄዱ ላለቁ ከ70 በላይ ኢትዮጵያውያን ሌላው ቢቀር ሰንደቃላማ እንኳን ዝቅ ብሎ እንዲውለበለብ አለመደረጉ በዜጎች መካከል ያለውን ልዩነት የሚየሳይ ነው በማለት አክለዋል። ( )
የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አያያዝ በአገራችን ፍትህ እንደሌለ የሚያሳይ ነው በማለት የፍትህ ስርአቱን የተቹት የመሰናዶ ተማሪዎች፣ አቶ አንዳርጋቸው ከስድስት ወራት የእስር ጊዜ በሁዋላ፣ በቤተሰብና በጠበቃ እንዳይጎበኙ፣ የታሰሩበትም እንዳይታወቅ መደረጉ የፍትህ ስርአቱ በአገራችን መቀበሩን ያሳያል ብለዋል።


Source: ESAT

የኢትዮጵያመከላከያሰራዊት‬ ገመና ሲጋለጥ



1)አስደንጋጩ አሀዝ
ባሰለፍነው 2006ዓ.ም መጨረሻ "የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊትን አጠቃላይ ይዞታና አቋም በተለይ ደግሞ ከነሐሴ 2003ዓ.ም እስከ ነሐሴ 2006ዓ.ም በሰራዊቱ የተከሰቱ አበይት ሁነቶችን " የግምገማ ውጤትን መሰረት አድርጎ እንደተዘጋጀ የተገለፀን ሪፖርት የማየት አጋጣሚን እንዳገኙ ከገለፁልኝ "የመከላከያ ሰራዊት ምንጮች " በአገኘውት መረጃ መሰረት "በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ስር ከሚገኙ ማለትም ከአራቱ የጦሩ እዞች፣አጋዚ ልዩ ኮማነዶን ጨምሮ ከተለያዩ የጦሩ ዲፓርተመንቶች እና ከሁሉም የጦር ማሰልጠኛ ኮሌጆች ስር ከሚገኙት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ውስጥ 13,895 የሚሆኑት ከነሐሴ 2003ዓ.ም እስከ ነሐሴ 2006ዓ.ም ድረስ ባለው ጊዜ ጦሩን ትተው ጠፍተዋል"
እነደ መረጃው ከሆነ ከ2003ዓ.ም እስከ 2006ዓ.ም ማለትም ለሶስት ዓመታት በአማካኝ በየቀኑ ከ12-13 የሚሆኑ የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አባላት ሰራዊቱን ትተው ጠፍተዋል፡፡
(የ"መከላከያ ሰራዊት ምንጮቸ "ያደረሱኝ መረጃዎችን በመመርኮዝ የጠፉትን ወታደሮች ለማግኘት ላለፉት ሶስት ዓመት ሲደረግ የነበረን ብዙም ያልተሳካ አሰሳንና ውጤቱን እንዲሁም ሌሎች ሁነቶችን በቀጣይ አቀርባለው)
ሀና መታሰቢያ ታህሳስ 2007

ሰበር ዜና !! ፖሊስ የደብረማርቆስ ተማሪዎችን እያፈሰ እያሰረ ነው




‹ኢህአዴግ አይገዛንም!›› ተማሪዎቹ
December 31 2014
ፖሊስ የ‹‹አብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ስልጠናን የተቃወሙ የደብረማርቆስ የመለስተኛ ሁለተኛ እና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ (መሰናዶ) ተማሪዎችን እያፈሰ እያሰረ እንደሚገኝ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ተማሪዎቹ በትናንትናው ዕለት ኢህአዴግን የሚተቹ አስተያየቶችንና ጥያቄዎችን በማንሳታቸው ይሰለጥኑበት ከነበረው ሰፊ አዳራሽ ወጥተው 20፣ 20 ሆነው በጠባብ ክፍል እንዲሰለጥኑ ከመደረጉም ባሻገር ጥያቄ የሚያነሱት ላይ ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
ዛሬ ጠዋት ጥያቄ ያነሳሉ የተባሉት ተማሪዎች ስልጠና ወደሚሰጡባቸው ትምህርት ቤቶች ግቢ እንዳይገቡ ከመደረጉም ባሻገር የድብዛ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች ስልጠናውን መቃወማቸውን ተከትሎ ፖሊስ እርምጃ እየወሰደ መሆኑን የሰሙ የተክለሀይማኖት መልስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እርምጃውን በመቃወም ለድብዛ ተማሪዎች ድጋፍ መስጠታቸው ተገልጾአል፡፡
የሁለቱም ትምህርት ቤት ተማሪዎች በጋር በመሆን ከተማው አደባባይ ላይ በመውጣት ‹‹አህአዴግ አይገዛንም፣ ኢህአዴግ ሌባ፣…›› የመሳሰሉ መፈክሮችን በማሰማት ተቃውሟቸውን መግለጻቸውን ተከትሎም ፖሊስ ተማሪዎቹን እያፈሰ ወዳልታወቀ ቦታ መውሰዱ ተሰምቷል፡፡ ከዚህም ባሻገር ጥያቄ የሚጠይቁና ፖሊስ ተቃውሞውን አደራጅተዋል ብሎ የሚጠረጥራቸውን ተማሪዎች እየፈለገ እያሰረ መሆኑን ተማሪዎቹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
በምስራቅ ጎጃም ዞን በ17ቱም ወረዳዎች የሚገኙ ተማሪዎች ስልጠናውን ካልወሰዱ ከትምህርት ቤት እንደሚባረሩና ፈተና ላይ እንደማይቀመጡ ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም ስልጠናውን መቃወማቸውን ምንጮቻችን ገልጸዋል፡፡

Tuesday 30 December 2014


የኢንተርኔት እና የተንቀሳቃሽ ስልክ መረጃዎች ላይ ጠበቅ ያለ ቁጥጥር የሚያደርግ አዋጅ ተረቀቀ
በሥራ ላይ ያለውን የብሮድካስት አዋጅ የሚሽርና ለመጀመሪያ ጊዜ በኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም ተንቀሳቃሽ ስልክን በመጠቀም የሚቀርብ የብሮድካስት አገልግሎቶችን ላይ ጥብቅ ቁጥጥር የሚያደርግ የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል፡፡የኢትዮጵያ የብሮድካስት ባለስልጣን ያዘጋጀውና በዚህ ዓመት ለፓርላማው ቀርቦ ይጸድቃል ተብሎ የሚጠበቀው ይህው የሚዲያ ረቂቅ አዋጅ አሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃን ማለትም ራዲዮ፣ቴሌቪዥን፣ የኢንተርኔት ድረገጾች እንዲሁም የሕትመት ሚዲያውን የሚመለከት ነው፡፡ በዚህ አዋጅ ለመጀመሪያ ጊዜ የአንተርኔት ድረገጾች ፈቃድ ማውጣት የግድ መሆኑን ደንግጎአል፡፡ 



Wednesday 24 December 2014

10 ቢሊዮን ብር በከንቱ ለባከነበት “የነፋስ ተርባይኖች” ቅሌት፣ ተጠያቂው ማን ነው?

“ለነፋስ ተርባይኖች” ግዢ በሚል ሰበብ በየአመቱ እንደዘበት የሚባክነው የቢሊዮን ብሮች ሃብት ሲታይ፣ በእርግጥም በኢትዮጵያ ታሪክ አቻ የማይገኝለት ቅሌት ነው ማለት ይቻላል። በየትኛውም አገር ቢሆን፣ በበለፀጉት አገራትም ጭምር፣ ከፍተኛ ሃብት በከንቱ እንዲባክን ማድረግ አሳፋሪ ተግባር ነው። አብዛኛው ህዝብ ችግረኛ በሆነባት፣ ሩብ ያህሉ ካለምፅዋት ሕይወቱን ማቆየት በማይችልባትና ገና አንገቷን ቀና ለማድረግ በምትውተረተር ደሃ አገር ውስጥ፣ በፈቃደኝነት ሃብት እንደ ዘበት ሲባክንስ ምን ይባላል?
Kenya-wind-energyእስካሁን በመቀሌና በአዳማ ናዝሬት የተተከሉት የነፋስ ተርባይን ጣቢያዎች፤ እንዲሁም በቅርቡ በተፈረመው ውል አዳማ ላይ የሚጀመረው ሦስተኛ የነፋስ ተርባይን ጣቢያ፣ በድምሩ 770 ሚሊዮን ዶላር (15.4 ቢሊዮን ብር) ገደማ ይፈጃሉ። ከዚሁ ገንዘብ ውስጥ፣ ከአስር ቢሊዮን በላይ የሚሆነው ሃብት በከንቱ የባከነ ነው። ለምን ቢባል፤ የነፋስ ተርባይኖቹ ዋጋ እጅግ ውድ ነው፤ ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅማቸው ደግሞ ደካማ! በሌላ አነጋገር፤ በአነስተኛ ወጪ የሃይል ማመንጫ ግድብ በመገንባት ከነፋስ ተርባይኖች በሶስት እጥፍ የሚበልጥ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ይቻላል። ነገሩ ቀልድ አይደለም።
አንደኛ፤ ብክነቱን በአንዳች “አሳማኝ ምክንያት” በይቅርታ እንድናልፈው ለማድረግ ይቅርና፤ በአንዳች “ማመካኛ” ለማድበስበስም አይመችም። ያፈጠጠ ብክነትና ያገጠጠ ቅሌት መፈፀሙ አያከራክርም። ወዲህ ወዲያ የሚያስብል ማምለጫ የለውም። ማንም ሊክደው የማይችል፣ ጎልቶ የሚታይና በቁጥር የተሰላ ሃቅ ነው። ሁለተኛ ነገር፣ የብክነቱ መጠን ያስደነግጣል – ከአስር ቢሊዮን ብር በላይ የአገር ሃብት ነው በከንቱ የባከነው። ከ40ሺ እስከ 50ሺ ኮንዶሚኒዬም ቤቶችን ሊያስገነባ የሚችል ሃብት! ወይም ደግሞ ባለፉት አስር አመታት ለነዋሪዎች ከተላለፉት ኮንዶሚኒዬም ቤቶች መካከል ግማሽ ያህሉን እንደማፍረስ ቁጠሩት።
የዚህ ጉደኛ ቅሌት መንስኤ፣ ሙስና ይሁን ሌላ ወንጀል፣ እብደት ይሁን ሞኝነት ማጣራት፤ የዋና ኦዲተር፣ የፓርላማ፣ የፖሊስ፣ የአቃቤ ህግ ሥራ ቢሆንም፤ ያን ያህልም አስቸጋሪ አይደለም። ከብዙዎቹ ቅሌቶች በተለየ ሁኔታ፣ እርቃኑን በግላጭ የሚታይ ግዙፍ ዘግናኝ አገራዊ ቅሌት ነውና። እንደገና ለማረጋገጥ ከፈለጋችሁ መረጃዎቹን እንደገና አንድ በአንድ መመርመር ትችላላችሁ። አለበለዚያ ደግሞ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል የሰጠውን ምላሽ ተመልከቱ – እውነታው ቁልጭ ብሎ ይታያችኋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ባለፈው ሳምንት በአዲስ አድማስ በሰጠው ምላሽ፤ አገሪቱ በነፋስ ተርባይኖች ኪሳራ ደርሶባታል ተብሎ የቀረበው ዘገባ የተጋነነ ነው ብሏል። ግን፣ በደፈናው “ተጋኗል” ከማለት ውጭ፤ የትኛው መረጃ እንደተጋነነ አልገለፀም። “ይሄኛው ወይም ያኛው መረጃ ተሳስቷል፣ ይሄኛው ወይም ያኛው ቁጥር ተዛብቷል” በሚል አንዱንም መረጃ ለማስተባበል አልሞከረም። በቁጥር የተሰላው የሃብት ብክነት ላይ፤ ድርጅቱ አንዳችም የቁጥር ማረሚያ ወይም ማስተካከያ አላቀረብም። ሊያቀርብም አይችልም። ለምን በሉ። መረጃዎቹ ትክክል ስለሆኑና የሃብት ብክነቱንም በግልፅ ስለሚያረጋግጡ ለማስተባበል አይመቹም። እንዲያውም፣ ራሱ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል በሰጠው ምላሽ፣ “በእርግጥ ከውሃና ከነፋስ ሃይል፣ ውዱ የነፋስ ሃይል ነው” ብሏል። ይህም ብቻ አይደለም። “ቀደም ባሉት ዓመታት በአብዛኛው በውሃ ላይ አተኩረን የቆየነው፣ ውሃ በርካሽ የገንዘብ አቅም መልማት ስለሚችል ነው” ብሏል – ድርጅቱ። ቀደም ብዬ እንደነገርኳችሁ፣ በነፋስ ተርባይኖች እና በኤሌክትሪክ ማመንጫ ግድብ መሃል ያለው ልዩነት፣ ፈፅሞ የሚያሻማ አይደለም። ጎልቶ የሚታይና በቁጥር የተሰላ ልዩነት ስለሆነ፣ ማንም ሊክደው አይችልም። የነፋስ ተርባይኖች በሙሉ፣ ኤሌክትሪክ የማመንጨት አቅማቸው ደካማ መሆኑ ሳያንስ፤ ወጪያቸው ከፍተኛ ነው። እስካሁን ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ የወጣባቸውን የነፋስ ተርባይኖች፤ እጅግ በዛ ቢባል 5 ቢሊዮን ብር በማይፈጅ የሃይል ማመንጫ ግድብ መተካት ይቻላል።
“መቼም፣ ሰዎች በጤና አይናቸው እያየ፣ ይህን ሁሉ ሃብት በከንቱ እንደዘበት ለነፋስ አይበትኑትም። አንዳች አሳማኝ ምክንያት ቢኖራቸው ነው” የሚል የቀቢፀ ተስፋ ምኞት ቢፈጠርባችሁ አይገርምም። አሳዛኙ ነገር፤ አንዳችም አሳማኝ ምክንያት የሚያቀርብላችሁ እንደማታገኙ በግልፅ እያያችሁት ይመስለኛል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ሃይል ድርጅት ይህንን እውነታ መካድ አልቻለም። እውነታው ምንድነው? የሃይል ማመንጫ ግድብ በመጠነኛ ወጪ የላቀ ውጤት ያስገኛል፤ የነፋስ ተርባይን በተቃራኒው ከፍተኛ ወጪ እየፈጀም ደካማ ነው!
ሃይል የማመንጨት ብቃታቸውን ለማነፃፀር ያህል፣ ባለፈው አመት ከሃይል ማመንጫ ግድቦችና ከነፋስ ተርባይኖች የተገኘውን የኤሌክትሪክ መጠን ተመልከቱ።
  • 2561
     
    Share
ከአሁን በፊት በተለያዩ አመታት መረጃዎችና በተለያዩ አገራት ጥናቶች እንደተረጋገጠው፣ የሃይል ማመንጫ ግድቦች ብቃት ከነፋስ ተርባይኖች ቢያንስ በ70 በመቶ ይበልጣል። የዘንድሮውን መረጃ ከሰንጠረዡ እንደምትመለከቱት ደግሞ፣ የሃይል ማመንጫ ግድቦች ብቃት ወደ ከነፋስ ተርባይኖቹ ወደ እጥፍ ገደማ ነው (በ100% ይበልጣል ማለት ነው)። በግንባታ ወጪ ስናወዳድራቸው ግን፣ በተገላቢጦሹ የነፋስ ተርባይኖች ግንባታ ለከፍተኛ ወጪ ይዳርጋሉ። የሃይል ማመንጫ ግድቦችን ለመገንባት ከሚወጣው ገንዘብ በእጥፍ የናረ ነው – የነፋስ ተርባይኖች ወጪ። ለአንድ ሜጋ ዋት የሚወጣውን ገንዘብ አነፃፅሩት።
በአጭሩ፤ ብቃታቸውን በቁጥር እናስተያይ ከተባለ፤ የሃይል ማመንጫ ግድብ ብቃት ከነፋስ ተርባይኖች ቢያንስ ቢያንስ በ70 በመቶ (ብዙውን ጊዜም በእጥፍ) ይልቃል። በወጪ ደግሞ በተቃራኒው፤ የነፋስ ተርባይኖች ከ100% በላይ (ከእጥፍ በላይ) ገንዘብ ይፈጃሉ። በድምር፤ የብቃትና የወጪ ልዩነታቸውን አዋህደን ስናነፃፅራቸው የሃይል ማመንጫ ግድቦች ውጤታማነት፣ አራት እጥፍ ያህል ነው – ከነፋስ ተርባይኖች ጋር ሲወዳደር።
በዚህ ስሌት ካሰብነው፣ እስካሁን ለተተከሉትና ውል ለተፈረመባቸው የነፋስ ተርባይኖች ከወጣው ወደ 16 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ውስጥ፣ 12 ቢሊዮን ያህሉ በከንቱ የባከነ ነው ማለት ይቻላል። ካሁን በፊት ባቀረብኩት ፅሁፍ ላይ ግን፣ የሃይል ማመንጫ ግድቦች ውጤታማነት ከሦስት እጥፍ በላይ መሆኑን፣ ለነፋስ ተርባይኖቹ የተመደበው ወጪም ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ፤ በከንቱ የባከነው ደግሞ ከአስር ቢሊዮን ብር በላይ እንደሆነ ነው የገለፅኩት። ለምን? “ተጋኗል” የሚል ማስተባበል እንዳይመጣ ለመከላከል በማሰብ ነው – የማስተባበያ ሰበቦችን ለማጥፋት።
ከመነሻው፣ በፅሁፌ ላይ የቀረቡት መረጃዎቹ ከአንድ ተከራካሪ ወገን የተወሰዱ አይደሉም። በጭራሽ አያከራክሩም። በኤሌክትሪክ ሃይል ድርጅት ሰነዶችና ጥናቶች ላይ በተደጋጋሚ በቁጥር የተገለፁ መረጃዎች ናቸው።
ምን ለማለት ፈልጌ ነው? የትኛው እንደሚሻልና የትኛው ለብክነት እንደሚዳርግ በግልፅ እየታወቀ ነው፤ ያ ሁሉ ሃብት እንዲባክን የተደረገው። እኮ ለምን? ግራ ያጋባል አይደል!
በአምስት ቢሊዮን ብር ወጪ የሃይል ማመንጫ ግድብ መገንባትና ተመሳሳይ የኤሌክትሪክ መጠን ማመንጨት እየተቻለ፣ ለምን ከ15 ቢሊዮን ብር በላይ ሃብት ለነፋስ ተርባይኖች ወጪ ይደረጋል? 50ሺ ኮንዶሚኒየም ቤቶችን ሊያስገነባ የሚችል ከአስር ቢሊዮን ብር የበለጠ የአገር ሃብት በከንቱ ማባከን ለምን አስፈለገ?
የድርጅቱ ምላሽ እነሆ – “በውሃ ላይ አተኩረን የቆየነው፣ ውሃ በርካሽ የገንዘብ አቅም መልማት ስለሚችል ነው። አሁን ግን የሃገራችን ኢኮኖሚ በማደጉ…”
ምን ምን? “ቀደም ሲል ብዙ ገንዘብ ስላልነበረን፣ ያለንን ገንዘብ ለሃይል ማመንጫ ግድብ እናውለው ነበር። አሁን ግን ብዙ ገንዘብ ስላለን በከንቱ ቢባክን ችግር የለውም” ለማለት ነው? አስገራሚ ነው።
“እንዲያውም” ይላል ድርጅቱ፤ “እንዲያውም ‘ውዱን ጭምር ለማልማት የቻለች፣ እያደገች ያለች ኢትዮጵያ’ ብላችሁ ነው መዘገብ ያለባችሁ”።እንዴት ነው ነገሩ! አድናቆት መሆኑ ነው? “ሃብትን በከንቱ ማባከን የቻለች አገር!” እንደማለትኮ ነው። አማራጮቹ ግልፅ ናቸው። እስቲ በቀላል አገላለፅ ለማነፃፀር እንሞክር። “15 ቢሊዮን ብር ለምን ተግባር ይዋል?” የሚል ጥያቄ ቀረበ እንበል። ለጥያቄውም ሁለት አማራጮች መጥተዋል።
እንደገና ልድገመው። የብክነቱና የቅሌቱ ማስረጃ የተሟላና ግልፅ ስለሆነ፤ ወዲህ ወዲያ የሚያስብል ማምለጫ የለውም – ማንም ሊክደው የማይችል፣ ጎልቶ የሚታይና በቁጥር የተሰላ ሃቅ ነው።
የብክነቱና የቅሌቱ መጠን ደግሞ ያስደነግጣል – ከአስር ቢሊዮን ብር በላይ የአገር ሃብት ነው በከንቱ የባከነው።
ገና ምላሽ ያላገኙ ሁለት ጥያቄዎች ግን አሉ። የቅሌቱ መንስኤ ምንድነው? የብክነቱ ተጠያቂዎችና የቅሌቱ ተዋናዮችስ እነማን ናቸው?
=========================================
ከውሃ ግድቦች የመነጨ               ከነፋስ ተርባይኖች የመነጨ ሃይል
ሃይል (ባለ 1810 ሜዋ)                (ባለ 171 ሜዋ)
አንደኛ ሩብ ዓመት        (2,070 ጊዋሃ)                      (100 ጊዋሃ)
ሁለተኛ ሩብ ዓመት      2,030 ጊዋሃ                             103 ጊዋሃ
ሦስተኛ ሩብ ዓመት      2,070 ጊዋሃ                          109 ጊዋሃ
አራተኛ ሩብ ዓመት      2,170 ጊዋሃ                          88 ጊዋሃ
የዓመት ድምር          8,340 ጊዋሃ                         400 ጊዋሃ
ከ1 ሜዋ የተገኘ         4 ጊዋሃ                             2.3 ጊዋሃ
የማመንጨት          ብቃት 52.6%                               26.7%
==================================
ከአሁን በፊት በተለያዩ አመታት መረጃዎችና በተለያዩ አገራት ጥናቶች እንደተረጋገጠው፣ የሃይል ማመንጫ ግድቦች ብቃት ከነፋስ ተርባይኖች ቢያንስ በ70 በመቶ ይበልጣል። የዘንድሮውን መረጃ ከሰንጠረዡ እንደምትመለከቱት ደግሞ፣ የሃይል ማመንጫ ግድቦች ብቃት ወደ ከነፋስ ተርባይኖቹ ወደ እጥፍ ገደማ ነው (በ100% ይበልጣል ማለት ነው)። በግንባታ ወጪ ስናወዳድራቸው ግን፣ በተገላቢጦሹ የነፋስ ተርባይኖች ግንባታ ለከፍተኛ ወጪ ይዳርጋሉ። የሃይል ማመንጫ ግድቦችን ለመገንባት ከሚወጣው ገንዘብ በእጥፍ የናረ ነው – የነፋስ ተርባይኖች ወጪ። ለአንድ ሜጋ ዋት የሚወጣውን ገንዘብ አነፃፅሩት።
==================================
የውሃ ሃይል ማመንጫ     አቅም             ጠቅላላ ወጪ            የ1 ሜዋ ወጪ
ተከዜ                      300 ሜዋ          340 ሚ. ዶላር         1.16 ሚ. ዶላር
ጣና በለስ                 460 ሜዋ           600 ሚ. ዶላር        1.3 ሚ. ዶላር
ግልገል ጊቤ2               420 ሜዋ          540 ሚ ዶላር          1.3 ሚ ዶላር
ግልገል ጊቤ3                1870 ሜዋ        1.7 ቢ ዶላር            ከ1 ሚ. ዶላር በታች
ሕዳሴ                        6000 ሜዋ       5 ቢ ዶላር              ከ1 ሚ. ዶላር በታች
የውሃ ሃይል ማመንጫ         አቅም             ጠቅላላ ወጪ           የ1 ሜዋ ወጪ
መቀሌ አሸጎዳ                  120 ሜዋ         300 ሚ ዶላር         2.5 ሚ ዶላር
ናዝሬት አዳማ1                51 ሜዋ           120 ሚ ዶላር          2.3 ሚ ዶላር
ናዝሬት አዳማ2                  153 ሜዋ         345 ሚ ዶላር        2.3 ሚ ዶላር
==============================
የ1 ሜዋ ወጪ
የሃይል ማመንጫ ግድቦች አማካይ ወጪ             1.1 ሚ. ዶላር
የነፋስ ተርባይኖች አማካይ ወጪ                    2.3 ሚ. ዶላር
==========================
ከአሁን በፊት በተለያዩ አመታት መረጃዎችና በተለያዩ አገራት ጥናቶች እንደተረጋገጠው፣ የሃይል ማመንጫ ግድቦች ብቃት ከነፋስ ተርባይኖች ቢያንስ በ70 በመቶ ይበልጣል። የዘንድሮውን መረጃ ከሰንጠረዡ እንደምትመለከቱት ደግሞ፣ የሃይል ማመንጫ ግድቦች ብቃት ወደ ከነፋስ ተርባይኖቹ ወደ እጥፍ ገደማ ነው (በ100% ይበልጣል ማለት ነው)። በግንባታ ወጪ ስናወዳድራቸው ግን፣ በተገላቢጦሹ የነፋስ ተርባይኖች ግንባታ ለከፍተኛ ወጪ ይዳርጋሉ። የሃይል ማመንጫ ግድቦችን ለመገንባት ከሚወጣው ገንዘብ በእጥፍ የናረ ነው – የነፋስ ተርባይኖች ወጪ። ለአንድ ሜጋ ዋት የሚወጣውን ገንዘብ አነፃፅሩት።
ምንጭ – አዲስ አድማስ

የተጠለፈው የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሔሊኮፕተር አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ

የኢትዮጵያ አየር ኃይል ንብረት የሆነ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ባለፈው ዓርብ ተጠልፎ ኤርትራ ግዛት አሰብ ማረፉ ተረጋገጠ፡፡ የዘወትር የበረራ ልምምድ ላይ የነበረውን የኢትዮጵያ አየር ኃይል ሩሲያ ሠራሽ ኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር ይዞ ወደ ኤርትራ የኮበለለው ዋና አብራሪ ሻምበል ሳሙኤል ግደይ፣ ይህንን ዓይነት ተግባር ይፈጽማል ብለው እንደማያስቡ ባልደረቦቹ ገልጸዋል፡፡
hlicopterከሻምበል ሳሙኤል ጋር በኢትዮጵያ አየር ኃይል አብረው የሠለጠኑና የሠሩ የሥራ ባልደረቦቹ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ግለሰቡ መልካም ባህሪ ያለውና በፖለቲካ አቋሙ ገለልተኛ የሚባል ነው፡፡ ‹‹እጅግ በጣም ጥሩ ሰው ነው፡፡ የመንግሥት ተቃዋሚ አልነበረም፡፡ ራሱን ከፖለቲካ ጉዳዮች የሚያገል፣ ሥራውን ብቻ የሚሠራና ልጆቹን በኃላፊነት የሚያሳድግ ሰው ነበር፤›› ብለው በድርጊቱ ግራ መጋባታቸውን ገልጸዋል፡፡
አክለውም በትንሽ ነገር የሚከፋና የሚደሰት፣ በቅጽበት የሚለዋወጥ ባህሪ እንዳለው ተናግረዋል፡፡ በግል ሕይወቱም የሚበሳጭበት ጉዳይ እንደነበርና አልፎ አልፎም በዚሁ ጉዳይ ይደበት እንደነበር አልሸሸጉም፡፡ ሻምበል ሳሙኤል ለሥልጠና ወደ ኢትዮጵያ አየር ኃይል የገባው በ1994 ዓ.ም. ሲሆን፣ የቅጥር ውል የፈረመው በታህሳስ ወር 1995 ዓ.ም. ነበር፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይልን ለ12 ዓመታት አገልግሏል፡፡ በ2003 ዓ.ም. የአገር መከላከያ ሚኒስቴር ወደ ዳርፉር ሱዳን ያሰማራው የሰላም አስከባሪ ኃይል አባል በመሆን ለአንድ ዓመት ያህል እንዳገለገለና በዚያም ተልዕኮ ዳጐስ ያለ ዶላር ይዞ መመለሱን ባልደረቦቹ ተናግረዋል፡፡
ሻምበል ሳሙኤል ተወልዶ ያደገው በትግራይ ክልል መቀሌ ከተማ መሆኑን፣ ወላጆቹ የመቀሌ ነዋሪ መሆናቸውን ባለቤቱና ሁለት ልጆቹ ቢሾፍቱ እንደሚኖሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ባለፈው ዓርብ ማለዳ ከረዳት አብራሪው መቶ አለቃ ቢልልኝ ደሳለኝና የበረራ ቴክኒሺያን ፀጋ ብርሃን ግደይ ጋር በኤምአይ 35 ተዋጊ ሔሊኮፕተር የዘወትር የልምምድ በረራ ለማድረግ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ድሬዳዋ ከሚገኘው የአየር ኃይል ቤዝ እንደተነሱ ለመረዳት ተችሏል፡፡ ዋና አብራሪው ከአጭር ጊዜ በረራ በኋላ የበረራ ከፍታውን በመቀነስ ወደ ኤርትራ በማቅናት ሔሊኮፕተሩን አሰብ ማሳረፉን ምንጮች ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
መከላከያ ሚኒስቴር ባለፈው ሰኞ ባወጣው መግለጫ ተዋጊ ሔሊኮፕተሩን ዋና አብራሪው ይዞ ወደ ኤርትራ መኮብለሉን አምኗል፡፡ ሚኒስቴሩ በመግለጫው ዋና አብራሪው ቴክኒሺያኑንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን አስታውቋል፡፡
ሔሊኮፕተሩ ባለፈው ዓርብ ከጠዋቱ 2፡35 ሰዓት ጀምሮ በመደበኛ የሥልጠና ልምምድ ላይ እንደነበር ጠቅሶ፣ ሔሊኮፕተሩ ከግንኙነት ውጪ በመሆኑ ሠራዊቱ በአካባቢው ማኅበረሰብና አጋሮች ለተከታታይ ቀናት ፍለጋ ሲደረግለት መቆየቱን አትቷል፡፡ ‹‹ሆኖም ሔሊኮፕተሩ በከሀዲው ዋና አብራሪ አማካይነት ቴክኒሻንና ረዳት አብራሪውን በማስገደድ ኤርትራ ማረፉን መረጃዎች ይጠቁማሉ፤›› ብሏል፡፡ ያነጋገርናቸው የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች ዋና አብራሪው የሔሊኮፕተሩ አዛዥ በመሆኑ የትም ወስዶ ሊያሳርፈው እንደሚችል ተናግረዋል፡፡
‹‹ረዳት አብራሪው ጀማሪ ነው፡፡ የበረራ ቴክኒሺያኑ ቴክኒካዊ ጉዳዮችን መከታተል ነው፡፡ ዋና አብራሪው ረዳት አብራሪውና ቴክኒሺያኑ እያወቁም ወይም ያለነሱ ዕውቅና የፈለገበት ወስዶ ሊያሳርፍ ይችላል፤›› ብለዋል፡፡ ባለፈው ወር የኢትዮጵያ አየር ኃይል ከፍተኛ አመራሮች ጠንከር ባለ ግምገማ ተወጥረው መክረማቸውን ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር መትረየስና ተወንጫፊ ሮኬቶች የተገጠሙለት ዘመናዊ ተዋጊ ሔሊኮፕተር ነው፡፡ ከኋላው ስምንት ወታደሮችን ወይም ሁለት የቁስለኛ አልጋዎችን መያዝ ይችላል፡፡ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ኤምአይ 17 እና ኤምአይ 8 የትራንስፖርት ሔሊኮፕተሮች ሲኖሩት፣ ለውጊያ የሚጠቀምባቸው በደርግ ጊዜ የተገዙ ኤምአይ 24 ሔሊኮፕተሮችን ነበር፡፡ በግንቦት 1990 ዓ.ም. የኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ሲጀመር አሥር ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተሮች የተገዙ ሲሆን፣ በጦርነቱ ወቅት ጥቅም ላይ ውለዋል፡፡
የ1997 ዓ.ም. ሦስተኛ ብሔራዊ ምርጫ ተከትሎ የተነሳውን ግርግር ተከትሎ ሁለት የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪዎች (ሻምበል አብዮት እና ሻምበል በኃይሉ) አንድ ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ይዘው ወደ ጐረቤት አገር ጂቡቲ መኮብለላቸው ይታወሳል፡፡ ብዙም ሳይቆይ የጂቡቲ መንግሥት አብራሪዎቹን አሳልፎ ለኢትዮጵያ መንግሥት የሰጠ ሲሆን ሔሊኮፕተሩንም መልሷል፡፡ አብራሪዎቹ የጦር ፍርድ ቤት ቀርበው በአሁኑ ወቅት በእስር እንደሚገኙ ለማወቅ ተችሏል፡፡
በተመሳሳይ ወቅት በቤላሩስ በሥልጠና ላይ የነበሩ ሰባት የኢትዮጵያ አየር ኃይል የኤስዩ 27 ተዋጊ ጀት አብራሪዎች ከድተው ጥገኝነት መጠየቃቸው ይታወሳል፡፡ አብራሪዎቹ በተለያዩ የምዕራብ አገሮች ጥገኝነት ማግኘታቸው ይነገራል፡፡
ቀደም ሲል ሻምበል ተሾመ ተንኮሉ የተባለ የአየር ኃይል ባልደረባ በ1995 ዓ.ም. ኤል 39 የተሰኘ የመለማመጃና ቀላል የውጊያ አውሮፕላን ለልምምድ በረራ ከመቀሌ ቤዝ ይዞ እንደተነሳ ወደ ኤርትራ ኮብልሎ ነበር፡፡
እስከ ማክሰኞ ታኅሳስ 14 ቀን 2007 ዓ.ም. ምሽት ድረስ የኤርትራ መንግሥት ስለተጠለፈው ኤምአይ 35 ሔሊኮፕተር ምንም ዓይነት መግለጫ አልሰጠም፡፡
source: zehabesha

Thursday 11 December 2014

የሳዑዲ አረቢያ ግብረ ሠናይ ድርጅት ሆስፒታል በኢትዮጵያ

የሳዑዲ ግብረ-ሠናይ ድርጅት ሆስፒታል በኢትዮጵያ

ድርጅቱ ቀደም ሲል ሆስፒታሉን አዲስ አበባ ዉስጥ ለመገንባት ጥያቄ ቢያቀርብም የከተማይቱ መስተዳድር ለሆስፒታሉ ማስገንቢያ የሚሆን መሬት ባለመፍቀዱ ትግራይ ዉስጥ ለማስገንባት ወስኗል።



አል ባስር የተሠኘ የሳዑዲ አረቢያ ግብረ-ሠናይ ድርጅት ሽሬ እንደ ስላሴ-ትግራይ ዉስጥ የዓይን ሕክምና መስጪያ ሆስፒታልና የሕክምና ባለሙያዎች ማሠልጠኛ ማዕከል ለመገንባት የመሠረት ድንጋይ አኖረ። ድርጅቱ ቀደም ሲል ሆስፒታሉን አዲስ አበባ ዉስጥ ለመገንባት ጥያቄ ቢያቀርብም የከተማይቱ መስተዳድር ለሆስፒታሉ ማስገንቢያ የሚሆን መሬት ባለመፍቀዱ ትግራይ ዉስጥ ለማስገንባት ወስኗል። ድርጅቱ ከትግራይ በተጨማሪ በኒ ሻንጉል፤ ሶማሊያ፤ ድሬዳዋና አፋር መስተዳድር ተመሳሳይ ሆስፒታሎች ለመገንባት አቅዷል። የአዲስ አበባዉ ወኪላችን ጌታቸዉ ተድላ ሐይለ ጊዮርጊስ ዝርዝር ዘገባ ልኮልናል።
source: DW

Sunday 7 December 2014

Security Message for U.S. Citizens in Ethiopia

December 6, 2014
U.S. Embassy Addis Ababa, Ethiopia | December 5, 2014
The U.S. Embassy informs U.S. citizens that political rallies or demonstrations may occur without significant notice throughout Ethiopia, particularly in the lead up to Ethiopian national elections in May 2015. Such rallies and demonstrations may be organized by any party or group and can occur in any open space throughout the country. In Addis Ababa, applications for permits to conduct rallies are often requested for Meskel Square or Bel Air Field. Please remember that even public rallies or demonstrations intended to be peaceful have the potential to turn confrontational and escalate into violence. You should, therefore, stay alert and avoid areas of demonstrations, and exercise caution if in the vicinity of any large gatherings, protests, or demonstrations.U.S. Embassy Addis Ababa, Ethiopia
The U.S. Embassy reminds U.S. citizens of the on-going threat of terrorist attacks in Ethiopia. U.S. citizens are reminded and encouraged to maintain heightened personal security awareness. Be especially vigilant in areas that are potential targets for attacks, particularly areas where U.S. and western citizens congregate, including restaurants, hotels, bars, places of worship, supermarkets, and shopping malls. Al-Shabaab may have plans for a potential attack targeting Westerners and the Ethiopian government, particularly in Jijiga and Dolo Odo in the Somali Region of Ethiopia, and Addis Ababa. Attacks may occur without warning.
Due to serious safety and security concerns, U.S. government personnel and their families are presently restricted from traveling to the following areas except as permitted on a case-by-case basis:
Ethiopian/Kenyan Border (Southern Ethiopia): In southern Ethiopia along the Kenyan border, banditry and incidents involving ethnic conflicts are common. Security around the town of Moyale is unpredictable, and clashes between Ethiopian forces and the Oromia Liberation Front (OLF) have been reported.
Ethiopia/Eritrea Border (Northern Ethiopia): Ethiopia and Eritrea signed a peace agreement in December 2000 that ended their border war. However, the border remains disputed. The border area is a militarized zone where there is the possibility of armed conflict between Ethiopian and Eritrean forces. U.S. government personnel are restricted from travel north of the Shire (Inda Silassie)-Axum-Adigrat road in the Tigray region of Ethiopia. Personnel are further restricted from travel north of the road from Dessie through Semera to the Galafi border crossing with Djibouti, including the Danakil Depression and the Erta Ale volcano. In January 2012, a group of foreign tourists were attacked near the Erta Ale volcano in the Afar region near the Eritrean border, approximately 100 miles southeast of Adigrat in the Danakil Depression. The attack resulted in five deaths, three wounded, and four people kidnapped. The victims were European and Ethiopian citizens. The two Europeans who were kidnapped were subsequently released. On February 15, 2012, Ethiopia, which blamed Eritrea for the attack, retaliated by striking military camps in Eritrea where the attackers were allegedly trained. This episode illustrates the continuing volatility of the border area.
Somali Region (Eastern Ethiopia): Travel to Ethiopia’s Somali regional state is restricted for U.S. government employees, although essential travel to the region is permitted on a case-by-case basis. Since the mid-1990’s, members of the Ogaden National Liberation Front (ONLF) have conducted attacks on civilian targets in parts of the Somali regional state, particularly in predominantly Ogadeni zones. Expatriates have been killed in these attacks. In 2010, the Government of Ethiopia initiated peace talks with the ONLF, which are ongoing. Despite these talks, incidents of violence continue to occur. Throughout 2013, skirmishes between the ONLF and regional government security forces took place. Some of these incidents involved local civilians. Al-Shabaab maintains a presence in Somali towns near the Ethiopian border, presenting a risk of cross-border attacks targeting foreigners.
Gambella Region (Western Ethiopia): Sporadic inter-ethnic clashes are a concern throughout the Gambella region of western Ethiopia. While the security situation in the town of Gambella is generally calm, it remains unpredictable throughout the rest of the region. Intensified conflict between Sudan and the Republic of South Sudan (RSS) has significantly increased refugee flows into Western Ethiopia. Travel to the border areas in the Beneshangul-Gumuz Region (Asosa) is restricted to major towns north of the area where the Great Ethiopian Renaissance Dam (GERD) is being constructed due to political sensitivity.
We strongly recommend that U.S. citizens traveling to or residing in Ethiopia enroll in the Department of State’s Smart Traveler Enrollment Program (STEP). STEP enrollment gives you the latest security updates, and makes it easier for the U.S. embassy or nearest U.S. consulate to contact you in an emergency. If you don’t have Internet access, enroll directly with the nearest U.S. embassy or consulate.
Regularly monitor the State Department’s website, where you can find current Travel Warnings, Travel Alerts, and the Worldwide Caution. Read the Country Specific Information for Ethiopia. For additional information, refer to the “Traveler’s Checklist” n the State Department’s website.
Contact the U.S. embassy or consulate for up-to-date information on travel restrictions. You can also call 1-888-407-4747 toll-free in the United States and Canada or 1-202-501-4444 from other countries. These numbers are available from 8:00 a.m. to 8:00 p.m. Eastern Time, Monday through Friday (except U.S. federal holidays). Follow us on Twitter and Facebook to have travel information at your fingertips.
The U.S. Embassy in Addis Ababa is located at Entoto Street, P.O. Box 1014. The Consular Section of the Embassy may be reached by telephone: +251-111-306000 or e-mail at consacs@state.gov, and is open Monday-Thursday, 7:30 a.m.-5:00 p.m. For after-hours emergencies, U.S. citizens should call +251-111-306911 or 011-130-6000 and ask to speak with the duty officer.
source: ECADF 

Thursday 4 December 2014

ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ አመክሮ ተከለከለች

December 4,2014


(ኢ.ኤም.ኤፍ) ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ “ሽብርተኛ” ተብላ በእስር ላይ የምትገኝ ሲሆን እንደማንኛውም እስረኛ ልታገኝ የሚገባውን አመክሮ ሳታገኝ ቀርታለች:: በመሰረቱ አመክሮ የሚሰጠው አንድ እስረኛ በ እስር ቤት ቆይታው ወቅት የሚያሳየው መልካም ባህሪ ተገምግሞ ለአንድ እስረኛ ከተፈረደበት አመት ተቀንሶ እንዲወጣ ይደረጋል:: ከቤተሰብ ያገኘነው መረጃ እንደሚያስረዳው ከሆነ ለርዕዮት አለሙ ሊሰጣት የነበረው የአመክሮ ቅፅ “ከጥፋቴ ታርሜያለሁ” የሚል ነው::

ከዚህ በፊትም “አጥፍቻለሁ ይቅርታ ይደረግልኝ” ተብሎ በፕሬዘዳንቱ አማካኝነት የሚደረገውን ሂደት ሳትቀበለው ቀርታ የይቅርታ ደብዳቤ አለማገባቷ ይታወሳል:: አሁን በቅርቡ ማድረግ የሚቻለውን “አመክሮ” ተቀብላ ቢሆን ኖሮ አሁን ከ እስር የምትወጣበት ወቅት እንደነበር ከቤተሰብ አካባቢ ያገኘነው ምንጭ አረጋግጧል::ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን በዚህ ጉዳይ ያነጋገራት ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኤጀንሲ የመጣ ሰው ነበር:: በውይይታቸው ወቅት “ከጥፋቴ ታርሜያለሁ” የሚለውን አባባል ለመቀበል አልቻለችም:: ምክንያቱም ሃሳቧን በጽሁፍ ስለገለጸች ነው “አሸባሪ” ተብላ የታሰረችው:: ከፌደራል ማረሚያ ቤቶች ኤጀንሲ የመጣውም ሰው “እንግዲያው አንቺ ከጥፋቴ ታርሜያለሁ” ብለሽ የማትፈርሚ ከሆነ እኛም አመክሮ አንሰጥሽም ብሏታል::

Wednesday 3 December 2014

Ethiopia issues unfamiliar investor warning over war and famine

Ethiopia issues unfamiliar investor warning over war and famine


Every country tapping the global sovereign bond market details the dangers investors face in its prospectus, often in a boilerplate section enumerating possible problems – such as fiscal deficits or taxation issues – that is largely ignored.

But the document sent by Ethiopia to international investors ahead of its foray into the global sovereign bond market is somewhat different. Far from a boilerplate, it includes a list of unfamiliar hazards, such as famine, political tension and war.

The document, seen by the Financial Times, is a sobering reminder of the risk of investing in one of Africa’s less developed nations. With gross domestic product per capita at less than $550 per year, Ethiopia is the poorest country yet to issue global bonds.

In the 108-page prospectus, issued ahead of its expected $1bn bond, Ethiopia tells investors they need 
to consider the potential resumption of the Eritrea-Ethiopia war, which ended in 2000, although it “does not anticipate future conflict”.

There is also the risk of famine, the “high level of poverty” and strained public finances, as well as the possible, if unlikely, blocking of the country’s only access to the sea through neighbouring Djibouti should relations between the two countries sour.

Addis Ababa, Ethiopia’s capital, also warns that it is ranked close to the bottom of the UN Human Development Index – 173rd out of 187 nations – and cautions about the possibility of political turmoil. “The next general election is due to take place in May 2015 and while the government expects these elections to be peaceful, there is a risk that political tension and unrest . . . may occur.”

But the long list of risks is not deterring investors, as ultra-low interest rates in the US, the UK, eurozone and Japan push sovereign wealth funds and pension funds into riskier countries in search of higher-yielding bonds.

Instead, some investors are focusing on the danger of a currency crisis. Addis Ababa has devalued its currency, the birr, twice over the past five years – by 23.7 per cent in 2010 and 16.5 per cent in 2011 – in an effort to win export competitiveness. Since then, the Ethiopian central bank has managed to slow the currency’s depreciation by intervening regularly in the market.

Addis Ababa has now told potential investors that “it may not be possible for the National Bank of Ethiopia to manage the exchange rate as effectively in the future as it has in the past” because of reduced hard currency reserves.

The country has reserves to cover only 2.2 months’ worth of imports – almost half the 4.3 months it had in 2010-11. “Failure to manage a steadily depreciating exchange rate may adversely affect Ethiopia’s economy . . . [and its] ability to perform obligations under” the bonds, it says.

The prospectus also reveals for the first time details of Ethiopia’s heavy dependence on Chinese loans to finance its infrastructure investment. Credit lines from China and Chinese entities accounted for 42 per cent of all external loan disbursements in 2013-14, and for 69 per cent in 2012-13.

“China has emerged as a key development partner,” the prospectus says, “often providing sizeable financing tied to infrastructure projects undertaken by Chinese firms.” Among those, telecoms groups ZTE and Huawei and a company the prospectus names as China Electric Power have lent Ethiopia more than $2bn over the past few years.

Lazard, the investment bank advising Addis Ababa on financial matters, declined to comment. The Ethiopian government did not respond to a request for comment. Investors said the bond was expected to price later this week at between 6 and 7 per cent.

finacial times

Saudi Billionaire to Invest $100 Million in Ethiopian Farm

Saudi Billionaire to Invest $100 Million in Ethiopian Farm

  • 75
    Share

Bloomberg News

December 03, 2014
Saudi Star Agricultural Development Plc, an Ethiopian company owned by billionaire Mohamed al-Amoudi, said it plans to invest $100 million in a rice farm in western Ethiopia next year to kick-start the stalled project.
Employees of Saudi Star rice farm work in a paddy in Gambella. Photographer: Jenny Vaughan/AFP via Getty Images
Employees of Saudi Star rice farm work in a paddy in Gambella. Photographer:
Jenny Vaughan/AFP via Getty Images
The company leased 10,000 hectares (24,711 acres) in the Abobo district in the Gambella region, where it’s based, in 2008 and bought the 4,000-hectare Abobo Agricultural Development Enterprise from the government 18 months ago for 80 million birr ($4 million). After delays caused by unsuitable irrigation design and contractor performance issues, Saudi Star wants to accelerate work in 2015 after a change of management, a redesign of the farm and a successful trial of rain-fed rice on 2,000 hectares at the formerly government-owned operation, Chief Executive Officer Jemal Ahmed said by phone.
“We have a very aggressive plan,” he said on Nov. 26 from Jimma, about 260 kilometers (162 miles) southwest of the Ethiopian capital, Addis Ababa. “If we’re able to do that we’ll be able to produce more.”
The project is part of a government plan formalized in 2010 to establish commercial farms on 3.3 million hectares of fertile land in sparsely populated parts of the country such as Gambella. Ethiopia expected to earn $6.6 billion a year from agriculture exports in 2015, according to a five-year economic plan published in 2010, though total goods exports last fiscal year brought in $3.3 billion.
Prime Minister Hailemariam Desalegn said in October 2013 that progress on the program had been “very slow.”

Billionaire Investor

Ethiopia-born al-Amoudi is worth $8.1 billion, according to the Bloomberg Billionaires Index, which ranks him as the world’s 157th richest person. His company built underground oil-storage facilities in Saudi Arabia and he owns Preem AB, Sweden’s largest crude oil refiner. Al-Amoudi is increasingly investing in formerly government-owned farms in Ethiopia, a nation where companies under his Midroc group operate the only commercial gold mine and built the largest cement plant in 2011.
Saudi Star’s $100 million investment will focus primarily on building irrigation infrastructure, including finishing the main canal from the more than 25-year-old Alwero Dam built by Soviet engineers, as well as a rice de-husking plant, storage silos and land clearing, according to Jemal.
An initial plan to have the farm divided into 3.75-hectare plots to produce rice from submerged paddy fields has been shelved as unworkable, he said. Only 350 hectares has been developed since 2008 on the land leased for 300,000 Ethiopian birr ($14,908) a year.

Economically Unviable

“It was not environmentally and economically viable, that’s why they were struggling, so we stopped that,” Jemal said. “We want to make it large-scale flood irrigation, not small ponds.”
Saudi Star’s revenue is
forecast
 to be about $60 million in 2016 once the irrigation system is developed, with 60 percent of the aromatic rice exported mainly to Arab nations on the Persian Gulf, Jemal said.
Hampering current harvesting are late rains and, for two days in October, unrest in Abobo town after violence between ethnic Anuak, who are indigenous to Gambella, and other Ethiopians. The company has Ethiopian soldiers guarding its compound and about 100 stationed nearby. Two Pakistanis and three Ethiopians employed by Ghulam Rasool & Co., a closely held Pakistani engineering company building the irrigation canal, died in April 2012 after an attack by a group of gunmen.

Security Addressed

The government has “taken care” of security issues, farm manager Bedilu Abera said while seated in one of the air-conditioned trailers that are now Saudi Star’s headquarters after they were moved from Addis Ababa.
Anywaa Survival Organization, a Reading, U.K.-based rights group, said in an Oct. 14 statement that land leases in Gambella have fueled conflict.
“The rush for land, water and other essential natural resources has become a curse for indigenous and minority peoples who barely have legal protection and redress,” it said.
Saudi Star says only two Anuak villages of huts with sweeping grass roofs lie just outside the project’s boundaries in deep forest. Some local residents complain they’ve not benefited from the investment and that they suffer collective punishment by the military.
“They used to kill people from the village,” Akea Ojullo, a 27-year old teacher, said in a Nov. 23 interview in Perbong village. “It got worse after the attack on Saudi Star,” he said.

‘Wrong Project’

The company plans to work with local residents by investing in workers, distributing rice and plowing land for them. “We know we’re creating job opportunities, transforming skills, training local indigenous Anuak, but there’s a campaign to have people perceive it as a wrong project,” Jemal said.
The farm still has the backing of officials, even though progress has been slow, Jemal said.
“The government wants the project to be a success and see more Gambella people be able to work and produce more,” he said. “That’s the big hope.”
Large, complex projects like Saudi Star’s need many years to produce results, Gambella President Gatluak Tut Khot said in an interview in Gambella town.
“We are not disappointed about the operation because we know that agricultural operations are very difficult,” he said. “We are giving them time in order to correct every mistake, overcome every obstacle, every challenge they face.”

Monday 24 November 2014

The agreement between Sudan n Ethiopia to weaken the opposition is started.

November 23, 2014 (EL-DABBA) – Sudanese authorities and popular bodies have evacuated two thousands Ethiopian nationals from the locality of El-Dabba in the Northern state following discovery of several Hepatitis and AIDS cases among them.
The commissioner of El-Dabba locality, Isam Abdel-Rahman, told Sudan Tribune that the security committee in the state conducted a random medical examination for several foreigners, saying 6 of the 15 Ethiopian nationals who were examined tested positive for Hepatitis C.
He added that another sample containing 54 Ethiopian nationals showed that 5 of them tested positive for the disease, saying they decided to transfer them to the capital, Khartoum and hand them over to the police department of passports and immigration to take the necessary action.
A source within the popular body El-Dabba Development Authority said the random examination revealed that 12 Ethiopians are infected with Hepatitis C while 2 others have tested positive for AIDS, pointing that residents of El-Dabba embarked on collecting signatures to remove foreigners from the locality.
The commissioner said that nearly 2000 foreigners had left the locality, adding there are only 10 foreigners currently residing in El-Dabba.
Eyewitnesses told Sudan Tribune that dozens of Ethiopians were seen leaving El-Dabba locality to Khartoum, saying that few of them are waiting to sell their household appliance before they leave.
The commissioner further pointed the local authorities put in place new measures requiring undergoing medical examination before hiring any foreigner worker.
Sudanese towns have recently seen large influx of illegal Ethiopian workers who enter the country through the porous border with Ethiopia.

source: http://www.sudantribune.com/spip.php?article53124