Wednesday 29 April 2015

the scandalous details surrounding the Clinton Foundation highlighted in the soon to be

ወይ ይች ሀገር!!
ሼህ መሀመድ ሁሴን አል አሙዲን ለክሊንተን ፋውንዴሽን በ2006 ዓመተ ምህረት 20 ሚሊዮን ዶላር መስጠታቸውን ፒተር ስዋይዘር የተባሉ ጸሀፊ በቅርቡ ለህተመት በሚያበቁት መጽሀፋቸው ላይ በይፋ አጋልጠዋል። (እንኳን 20 ለምን 200 ሚሊዮን ዶላር አይሰጣቸውም? ብለን ዝም እንዳንል፤ ስጦታው የተሰጠው በኢትዮጵያ መንግስት ስም መሆኑ ያማል።ይህንንም አል አሙዲ -ለፋውንዴሽኑ በጻፉት ደብዳቤ አረጋግጠዋል። ለምን በኢትዮጵያ መንግስት ስም ሰጡ? የስጦታው ምክንያት ምንድነው?የሚል ጥያቄ ከተነሳ፤ አል አሙዲ በዚያው በስጦታ ደብዳቤያቸው ላይ ፦የቡሽ አስተዳደር የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ-በክሊንተን ጊዜም ሳይቀየር እንዲቀጥል መማጸናቸው(መጠየቃቸው)ተመልክቷል።
ያንንም ተከትሎ በባለቤታቸው ስም ገንዘቡን የተቀበሉት የወቅቱ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ሄላሪ ክሊንተን የአሜሪካ መንግስት በኢህአዴግ ላይ ማእቀብ እንዲጣል ያረቀቀው አዋጅ እንዲሰረዝ ፣ ይልቁንም አሜሪካ ለኢህአዴግ አስፈላጊውን እርዳታ እንድትሰጥ ማስደረጋቸውን ደራሲው አጋልጠዋል።
(እየተዛቀ የሚወጣው የሻኪሶ (የሀገሬ)ወርቅ፤ ሀገሬን ለማፈን እንደሚውል መስማት እንዴት ያማል!!!)
“ኢህአዴግ እንድሆን ያጠመቀኝ አሰፋ ማሞ ነው” አል-አሙዲ
ለማንኛውም ይህ የአል አሙዲን እና የክሊንተን ጉዳይ በፎክስ ኒውስ ሰፊ ሽፋን ያገኘ ወቅታዊ አጀንዳ ሆኗል። ሊንኩ ከታች አለ፤ ያዳምጡት፦ አረዳው ፎክስ ኒውስ ትልቅ አጀንዳ ነው የሰጠህ። ለጊዜው እገሊትና እገሌን ተዋቸውና ይህን ጉዳይ ተወያይበት፣ተነጋገርበት..ከዚህ (ከሀገር)የሚበልጥ አጀንዳ የለም።

 http://www.realclearpolitics.com/…/fox_news_special_the_tan…
ማህሌት ፋንታሁን
- ሙሉ ልብሴን እንዳወልቅ ተገድጄ ራቄቴን በወንድ መርማሪዎች ፊት ስፓርት አንድሰራ እገደድ ነበር ፡፡ “ሴትነትሽ አንዲህ ከሚዋረድ አመጽ እንዳነሳሳሽ እመኚ ተብያሁ”
- በሌሊት ግርፋት የሚፈጸምበት ክፍል ውስጥ ገብቼ ጫማሽን አውልቂ ተብዬ ጫማዬን አውልቄ ከቆምኩ በኋላ ውስጥ እግርሽን ከምትገረፊ አመጽ ማነሳሳትሽን አምነሽ ፈርሚ ተብያለሁ፡፡
- ሰጠሁት የተባለው ቃል ሰዎች በሚቀጥለው ክፍል እየተደበደቡ የጩኀት ድምጻቸው እየተሰማ ፈርሚ ተብዬ የተባልኩት ቦታ ላይ ሳላነብ በፍርሃት ፈርሜያለሁ።
- በተለያዬ ምርመራ ወቅቶች "ለነጭ አገሪትዋን የሸጥሽ ሸርሙጣ ውሻ ባንዳ..." አንዲሁም ለመጸፍ የሚከብዱ አፀያፈ ስድቦች በየቀኑ እሰደብ ነበር ፡፡
(*ይህ ጽሁፍ ለኢትዬጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው)

Saturday 25 April 2015

Anniversary of Arrest of Ethiopia’s Journalists

US State Dept. on Anniversary of Arrest of Ethiopia’s Journalists

April 24, 2015
STATEMENT BY MARIE HARF, ACTING SPOKESPERSON
Anniversary of the Arrest of Ethiopia’s Zone 9 Bloggers and Three Journalists
Tomorrow, April 25, marks one year since Ethiopia arrested six Zone 9 bloggers and three other journalists. These nine individuals—Befekadu Hailu, Zelalem Kibret, Atnaf Berhane, Natnael Feleke, Mahlet Fantahun, Abel Wabella, Asmamaw Hailegiorgis, Edom Kassaye, and Tesfalem Waldeyes—joined 10 other journalists already imprisoned in Ethiopia, bringing the total number of jailed journalists in Ethiopia to 19, including two Eritrean nationals. This is more than any other country in Africa. In July 2014, Ethiopian authorities charged the six bloggers and three journalists with terrorism under its Anti-Terrorism Proclamation. Their trial is ongoing. Ethiopia also charged one other Zone 9 blogger—Soliyana Shimelis—who was out of the country when her colleagues were arrested, with terrorism, in absentia. Soliyana has been unable to return to Ethiopia and, along with dozens of other Ethiopian journalists, now lives in exile.
Restrictions on press freedoms are inconsistent with the rights outlined in the Ethiopian constitution. Space for media, civil society organizations, and independent voices and views are crucial for democratic progress, development, and economic growth. While we recognize a judicial process is underway, we urge the Ethiopian Government to release journalists and other individuals imprisoned for exercising their right to freedom of expression, particularly those imprisoned who may merit humanitarian release on medical grounds. We urge Ethiopia to refrain from using its Anti-Terrorism Proclamation as a mechanism to curb the free exchange of ideas.
http://ecadforum.com/2015/04/24/us-state-dept-on-anniversary-of-arrest-of-ethiopias-journalists/ 

Friday 24 April 2015

ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው

” ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው Professor Berhanu Nega
የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ
የተከበራችሁ ወገኖቼ፤ ከሰላሳ በላይ የሆኑ ወገኖቻችን አይ ሲስ በተሰኘ ህሊና ቢስ፣ ፀረ-ሰው እና ፀረ-ስልጣኔ ቡድን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ የመገደላቸው መርዶ ከትናንት ወዲያ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓም ደርሶን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት በመሪር ሀዘን ውስጥ ነን። ዛሬ “እግዜር ያጥናህ” ወይም “እግዜር ያጥናሽ” የሚባል ሰው የለም። ሁላችንም ሀዘንተኞች ነን። ካጣናቸው ቁጥራቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ወገኖቻችን አሁንም በአራዶች መዳፍ ውስጥ መሆናቸው ሀዘናችን እጅግ የበረታ ያደረገዋል። ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ሆኖም በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ሊቢያ ውስጥ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሁንም ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ናቸው። ሌሎች በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ደግሞ በየመን ከሰማይም ከምድርም በቦንብና በጥይት እየተማገዱ ነው።
ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች ስብዕናችንን ገፈፉን።
የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?
በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው። እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።
ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።
ወገኔ፤ ዛሬ ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤ እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።
የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።
ብርሀኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር
ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም

Thursday 16 April 2015

እስከመቼ በማዘን እና በቁጭት እንኖራለን???

ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ሰሞኑን የጀመረው የውጪ ዜጎችን ኢላማ ያደረገው ጥቃት ተባብሶ መቀጠሉ ተነገረ፡፡ የበርካታ ሀገራት ዜጎች በስለት እታረዱ፣ በእሳት እየተቃጠሉ፣ ንብረታቸው እየተዘረፈና እየወደመ እንዲሁም እየተገደሉ እንደሚገኝ በርካታ የአለም ሚዲያዎች ዜናውን በመቀባበል ላይ ይገኛሉ
ኬንያ ውስጥ ኢትዮጵያኖች በጅምላ እየታሰሩ ነው። ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ኢትዮጵያኖች እየተደበደቡ ፤ በድንጋይ እየተፈነከቱ ፤ በዐይን እንኳን ለማየት በሚሰቀጠጥ ሁኔታ ጎማ ታስሮባቸው ቤንዚል ተርከፍክፎባቸው በእሳት እየተቃጠሉ ነው። የመን ውስጥም እንዲሁ ያለምንም ርህራሄ ኢትዮጵያኖች በግፍ እየተጨፈጨፉ ነው። አምና በሳውዲዎች ላይ "እነዚ እርኩስ አረቦች" እያልን ፀጉር ስንነጭ ፤ ዛሬም "እነዚህ አውሬ ጥቁሮች" እያልን ብናማርር ነገ የወገኖቻችንን እጣ ፈንታ ከዚህ የከፋ ሊሆን ይችላል እንጂ በ"RIP" እና ሌሎች ላይ የስድብ ናዳ በማውረድ ለውጥ አይመጣም።
.
ለዚህ ሁሉ ስደት ፣ ውርደት ፣ ግድያና ሰቆቃ የዳረገን የህወሃት አገዛዝ መሆኑን መገንዘብ አቅቶናል?! ህንድ ፣ ጅቡቲ ፣ ሱዳን እና ሱማልያ ሳይቀሩ ፥ ከነዚህ ሀገራት የራሳቸውን ዜጎች ሲያስወጡ ፤ የኛን ወገኖች ሊያድን ፍላጉቱም አቅሙም ያለው መንግስት የሚባል አካል አለመኖሩ አያንገበግበንም!?
እስከመቼ በማዘን እና በቁጭት እንኖራለን ?? እውነት በወገኖቻችን ጭፍጨፋ ያዘንን ከሆነ ቢያንስ የተደራጁ ሀይሎችን እንርዳ ፣ እናጠናክር ፤ ውርደት ይበቃል እንበል!!



Monday 13 April 2015

እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ የርሃብ አድማ መቱ

እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ የርሃብ አድማ መቱ
በማዕከላዊ እስር ቤት ታስረው የሚገኙት ብርሃኑ ተክለያሬድና ፍቅረ ማሪያም አስማማው አብራቸው በታሰረችው እየሩስ ተስፋው ላይ እየተፈፀመ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በመቃወም የርሃብ አድማ መቱ፡፡ ብርሃኑና ፍቅረማሪያም ከትናንት የትንሳኤ በዓል ጀምረው የእርሃብ አድማ ያደረጉ ሲሆን በትናንትናው ዕለት የገባላቸውን ምግብ እንዳልበሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
እየሩሳለም ተስፋው ከሳምንት በላይ ብቻውን እንድትታሰር ተደርጋ ከፍተኛ ምርመራ እየተደረገባት ሲሆን ከቤተሰቦቿ ጋር እንዳትገናኝ ተደርጋለች፡፡ የማዕከላዊ ምርመራ ጥበቃ ፖሊሶች ቤተሰቦቿ ስለ እየሩስ በሚጠይቁበት ወቅት ‹‹መግባት አይቻለም›› ከማለት ውጭ ምክንያቱን እንደማይናገሩም ከቤተሰቦቿ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡
እነ ብርሃኑ እየሩስ ተስፋው ላይ እየተፈፀመ ያለው ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እስካልቆመ ድረስ የርሃብ እድማቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡

ወያኔ ካለው በላይ የሚያሳይና ከሚያውቀው በላይ የሚናገር ግብዝ መንግስት መሆኑ....

ዜና /01 07 2007 ዓ.ም
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ በወያኔ መንግስት ላይ ማንኛውንም ኃይል ወይንም የአፀፋ ግብረ ኃይል በየትኛውም፣ ጊዜ በማናቸውም ቦታ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ፡፡
ሰሞኑን ወያኔ እየፈፀመው ከሚገኘው ከፕሮፖጋንዳ ፍጆታነት የማያልፍ የአየር ላይ ተዋጊ አውሮፕላን ትርኢት፣ የእግረኛና የሜካናይዝድ ውጊያ ልምምድና ከቦታ ቦታ የሠራዊት ጉዞ አንፃ የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ወታደራዊ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር አሰፋ ማሩ
“ወያኔ ካለው በላይ የሚያሳይና ከሚያውቀው በላይ የሚናገር ግብዝ መንግስት መሆኑ ምንጊዜም ቢሆን መዘንጋት የለበትም፡፡” ብለዋል፡፡
ኮማንደር አሰፋ አያይዘውም
“ወያኔ ሁለቱም እግሮቹ ከጉልበቱ ላይ እሱ የህዝቡን አንገት ለመቅላት ከዘር ሰገባ በመዘዘው ስለታም ሰይፍ ተቆርጠው ቁመቱ እጅግ በጣም ድንክ ሆኗል፡፡ ሰው ሰራሽ እግሮች ቀጥሎ ወደ ላይ በመንጠራራት ነው ያደገ ለመምሰል እየሞከረ የሚገኘው፡፡
በህዝቡ ፊት የሚያደርጋቸው ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች የምናብ ፈጠራ ፍሬዎች እንጂ የጦር ሜዳ ዓለም ነፀብራቆች አይደሉም፡፡ አንድ ገበሬ ገና ለገና ንብ ይገባልኛል ብሎ ተስፋ በማድረግ ብቻ በእበት ለቅልቆ በሰም ጭስ በማጠን ትልቅ ዛፍ ላይ በሰቀለው ባዶ ቀፎ የሚመሰለው ህወሓት ያሁን ጊዜ እንቅስቃሴዎቹ ሁሉ በራስ ካለመተማመንና ከፍርሃት የመነጩ ናቸው፡፡ ዛፍ ላይ የተሰቀለ ባዶ ቀፎ ንብ ሳይኖረው ማር በውስጡ ሊከማችበት አይችልም፡፡ መምሰልና መሆን ልዩነታቸው የትየለሌ ነው፡፡ ደግሞም እዩኝ እዩኝ ያለ ቆይቶ ደብቁኝ ደብቁኝ ማለቱ ሳይታልም የተፈታ ነው፡፡” በማለት ገልፀዋል፡፡
ኮማንደሩ እንዳሉትም ወያኔ በእንድ መልክ በወታደራዊ አቅሙ የተባ መስሎ ለህዝቡ ለመታየት ይጣጣራል፤ በሌላ መልኩ ደግሞ እንደ ሸንኮራ መጥጦ ከተፋቸው የቀድሞ ሠራዊት አባላት እግር ስር ሳይቀር እየወደቀ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የህወሓት ጀነራሎች በየመንደሩ እየዞሩ የገበሬ ታጣቂዎችን ዘበመሰብሰብ
“ጦርነት ዓይኑን አፍጥጦ መጥቶብናል፤ ሠራዊታችን እየፈረሰ ወደ ኤርትራ በመኮብለልና የታጠቁ ቡድኖችን በመቀላቀል መዋጋት እንደማይፈልግ አቋሙን እየገለፀልን ነው፡፡ እባካችሁን ባይሆን እናንተ እርዱን አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርግላችኋለን፡፡” እያሉ በመማፀን ላይ እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የአርበኞ ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ወታደራዊ አዣዥ ከማንደር አሰፋ ማሩ
“አርበኞች ግንቦት 7 ህዝቡ እንዲያደርግ የሚፈልገውንና የሚጠበቅበትን ማንኛውንም ተግባር ሁሉ በአስፈላጊው ጊዜና ቦታ ለመፈፀም ዝግጁ ነው፡፡” ካሉ በኋላ
“ህዝቡ ደግሞ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የተጫነውን የባርነት ቀንበር አልሸከምም ብሎ እምቢተኛ መሆንና የትጥቅ ትግሉን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከመደገፍ ባለፈ በባለቤትነት ማስኬዱን በተጠናቀረ ሁኔታ መቀጠል አለበት፡፡” ሲሉ የኢትዮጵያን ህዝብ አሳስበዋል፡፡
በማህበራዊ ድረ-ገፆች አማካኝነት ነፃነት በተራቡ ወጣቶች ቀስቃሽ ነት የተጀመረው ዝርዝር ሳንቲሞችን በመሰብሰብ ለወያኔ መንግስት ፍፁም አምባገነናዊ አገዛዝ እምቢተኛነትን የመግለፅ ሂደቱ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡
በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ከተሞች የሚኖሩ እምቢተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች በትንሹ የ3 መቶና የ4መቶ ብር ሳንቲሞች በየጓዳው እያከማቹ ተቃውሟቸውን በመግለፅ ላይ ይገኛሉ፡፡ አንድ ብር በ0.75 ሳንቲም መመንዘር የጀመረባቸው ከተሞች እንዳሉም ታውቋል፡፡

Wednesday 8 April 2015

Our beloved `terrorists`!!!!!!


Our beloved `terrorists` still smile even if they are facing fabricated charges. who can be scared of these harmless girls for blogging? Tplf is living in fear! they are even scared of these nice bloggers and activists! Tplf should be liberated from its extreme fear and freedom-phobia so that all bloggers, journalists and activists will also be freed and live in peace.

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ከጎንዬሽ ጉዳዬች ውጪ ለ25ተኛ ጊዜ (በአጠቃላይ ለ27ተኛ ጊዜ) የተሰየመው ችሎት ዛሬም የደረጃ ምስክሮችን ሲያሰማ ውሏል፡። ከሳምነትት በፌት የተሰየመው ችሎት አቃቤ ህግ 41 ምስክሮች አሉኝ ነገር ግን ላገኛቸው ስላልቻልኩ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ቆይተው ተጨማሪ ማፈላለጊያ ጊዜ ይሰጠኝ በማለት ጠይቆ ለዛሬ የተቀጠረ ቢሆንም ዛሬም “የሽብር ተግባሩ “ ዋና ምስክሮች ባለመገኘታቸው ፍተሻ ላይ ተገኝተናል ያሉ አምስት ምስክሮች ተሰምተዋል፡። የምስክሮቸን ቁጥርም 35 ነው በማለት ቀይሮታል፡፡
ባለፈው የተሰሙት 13 ምስክሮች ሲሆኑ በዛሬው ችሎት ባልተካደ ነገር ላይ ሲመሰክሩ የዋሉት የደረጃ ምስክሮች 
14ተኛ ምስክር ተወዳጅ ኃ/ማርያም ይባላሉ፡፡ እድሜያቸው 34 ሲሆን የመንግስት ሰራተኛ ናቸው፡፡ የምስክርነት ቃላቸውም ‹‹የመጣሁበት ኬዝ ግንቦት 7/2006 ዓ.ም በምኖርበት ልደታ 5ኛ አካባቢ የፌደራል ፖሊስ ታዛቢ ሁነኝ ብሎ ጠይቆኝ በታዛቢነት ያየሁትን ለመመስከር ነው፡፡ ማህሌት ጤና ጥበቃ ሚ/ር ትሰራለች መሰለኝ፣ እዚያ መስሪያ ቤት ፖሊስ ማህሌት ኮምፒውተርና ጠረጴዛ ላይ ያለውን ሲበረብር አይቻለሁ፡፡ መንግስት መስሪያ ቤት የምትጠቀምበት ኮምፒውተር ላይ የተገኙ ሰነዶች ላይ ማህሌት ስትፈርም እኛ ታዛቢዎችም ፈርመናል፡፡ የፈረምነው ግንቦት 7/2007 ዓ.ም ነበር፡፡ የገጹን ብዛት አሁን አላስታውስም፤ ወደ 40 ገጽ ይሆናል፡፡ እንግሊዝኛና አማርኛ ጽሁፎች አሉበት፡፡ የተወሰነ የፖለቲካ ይዘት የነበረው አለ፡፡ የፖለቲካ ፕሮግራም ማኒፌስቶ አይቻለሁ፡፡ ፖሊስ ማህሌትን ሲጠይቃት ከኦነግ የወጣው የሌንጮ ፓርቲ ፕሮግራም ነው ብላለች፡፡ ጎስፕ ንግግሮችም አሉ›› ብሏል፡፡ ዳኛው ጎሲፕ በአማርኛ ምንድነው ሲላቸው ምስክሩ ‹‹ሽሙጥ ንግግር ነው›› ብለው መልሰዋል፡፡ ምስክሩ የተገኙ ሰነዶች ላይ ፌደራል ፖሊስ ሄደው እንደፈረሙና ይሄን ያደረጉትም ግንቦት 9/2006 ዓ.ም ነው ብለዋል፡
15ተኛ ምስክር ፀሐይ ብርሃኔ እድሜያቸው 33 የሆኑ የመንግስት ሰራተኛ ናቸው፡፡ የምስክርነት ቃላቸውም ‹‹ግንቦት 7/2006 ዓ.ም ከቀኑ 4፡00 ፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ፖሊስ የፍርድ ቤት ትዕዛዝ አሳይቶ ቢሮ ሲፈተሽ ታዘብ ተብዬ ተገኝቼ ነበር፡፡ ሲ.ዲ እና ዲክሜንት ሲወሰድ አይቻለሁ፡፡ ከዚያ ፖሊስ በ9/2006 ዓ.ም ሄጄ በሶፍት ኮፒ የነበሩት ሰነዶች ፕሪንት ተደርገው ማህሌት የፈረመችባቸው ላይ ፈርሜያለሁ፡፡ በእንግሊዝኛና አማርኛ የተጻፉ ናቸው፡፡ በግምት ወደ 40 ገጽ ይሆናል፡፡ አብዛኛው የፖለቲካ ነክ ጽሑፎች ናቸው፡፡ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ጽሑፎች አሉበት፡፡ ያየናቸው መረጃዎች ከእሷ ኮምፒውተር ላይ ስለመገኘታቸው አይተን ፈርመናል፡፡››
ለእኒህ ምስክር መስቀለኛ ጥያቄዎች ቀርበውላቸው ነበር፡፡
የጠበቆቹ መስቀለኛ ጥያቄ፡- ሲዲውን ማን እንዳመጣው
ታውቃለህ…ውስጡ ምን ነበረበት…
የምስክሩ መልስ፡- እኛ ራሳችን ቼክ አድርገናል፤ ባዶ ሲ.ዲ ነው፡፡
ጥያቄ፡- የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ብለሃል….ስንት ናቸው
መልስ፡- አንድ ብቻ አይደሉም
ጥያቄ፡- የተለያዩ ፓርቲዎች ሰነዶች ብለዋል እኮ….እነዚህ ላይ ሁሉ ፈርመዋል
መልስ፡- አሁን በትክክል የማስታውሰው የሌንጮ ፓርቲ ሰነድ ላይ መፈረሜን ነው፡፡ ሌሎች ላይ አልፈረምኩም፡፡
(አንድ ሰነድ ቀርቦላቸው ፊርማው የእሳቸው ስለመሆኑ እንዲለዩ ተደርገው የእሳቸው መሆኑን አረጋግጠው የፈረሙበትን ሰነድ ይዘት ግን እንደማያውቁ አስረድተዋል፡፡)
ፍርድ ቤቱ ‹‹40 ገጽ ማየትህን ተናግረሃል፤ 40 ገጽ ላይ ፍርመሃል፣ ይዘቱንስ ታውቃለህ›› ብሎ ጠይቋቸው ምስክሩ ‹‹እያንዳንዱ ሰነድ ላይ ፍረሜያለሁ፤ ግን አላነበብኩትም፡፡ ክፍት የስራ ማስታወቂያ የሚል ግን አይቻለሁ›› ብለዋል፡፡ በተለየ የትኛውን ነው ያነበብከው ለተባሉት ደግሞ ‹‹አሁን አላስታውስም፤ የሌንጮ ሰነድ ላይ ፈርሜያለሁ፡፡ ማህሌት ፖሊስ ሲጠይቃት ሌንጮ የራሳቸውን አዲስ ፓርቲ እያቋቋሙ እንደሆነ ስትናገር ሰምቻለሁ›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡
16ተኛ ምስክር ዳግማዊ እንዳለ 25 ዓመታቸው ሲሆን የመንግስት ሰራተኛና የአ.አ ከተማ የካ ክ/ከተማ ነዋሪ ናቸው፡፡ በ5ኛ ተከሳሽ አጥናፍ ላይ ለመመስከር እንደመጡ ተናግረው የአባቱን ስም አላስታውስም ብለዋል፡፡
“ሚያዝያ 17/2006 ዓ.ም 11፡00 ገደማ ከስራ ወደ ቤት ስሄድ 22 ትራፊክ ፖሊስ ጀርባ ፌደራል ፖሊስ የፍርድ ቤት ወረቀት አሳይቶ ታዛቢ ሁነኝ ብሎኝ ተገኝቻለሁ፡፡ አጥናፍ ቤት ገብተን ሰነዶች ሲገኙ አይቻለሁ፡፡ ፍላሽ፣ ሴኪዩሪቲ ኢን ኤ ቦክስ የሚል መጽሐፍ፣ ሲ.ዲ ተገኝተዋል፡፡ ሌሎች ታዛቢዎችም ነበሩ፡፡ ሰነዶቹ ላይ አጥናፍ ሲፈርም እኛም ፈርመናል፡፡›› ብለዋል፡፡
17ኛ ምስክር፡- ሳምሶን ሲሳይ ይባላሉ፤ 29 ዓመታቸው ሲሆን በግል ስራ ላይ የተሰማሩ ናቸው፡፡ አድራሻቸው አ.አ የካ ክ/ከተማ ነው፡፡ አጥናፍ ላይ ለመመስከር መምጣታቸውን ተናግረዋል ‹‹ሚያዝያ 17/2006 ዓ.ም 11፡00 አካባቢ ትራፊክ ጽ/ቤት ጀርባ ፖሊሶች ታዘብልን ስላሉኝ ታዝቤያለሁ፡፡ ሲ.ዲ፣ ፍላሽ፣ የተለያዩ ዶክሜንቶች፣ ላፕቶፕ፣ ማስታወሻ ደብተሮች መገኘታቸውን አይቻለሁ፡፡ በዝርዝር አላስታውስም፡፡ ግን 150 አካባቢ መጽሐፍ ቆጥረናል፡፡ ፋክት መጽሔት ተገኝቷል፡፡ መጽሐፎቹ በእንግሊዝኛና አማርኛ የተጻፉ ናቸው፡፡ አጥናፍ የፈረመባቸው ላይ እኛም ፈርመናል፡፡›› ብለዋል፡፡
18ኛ ምስክር፡- እኒህ ምስክር ደግሞ በረከት ብርሃኔ የሚባሉ ሲሆን እድሜያው 29 ነው፡፡ በግል ስራ ላይ የተሰማሩና የአ.አ አራዳ ክ/ከተማ ነዋሪ ናቸው፡፡ 6ኛ ተከሳሽ ዘላለም ላይ ለመመስከር እንደመጡ በመግለጽ ዘላለምን በአካል ለይተው አሳይተዋል፡፡ ‹‹ግንቦት 16/2006 ዓ.ም ማዕከላዊ ለግል ጉዳይ ሄጄ ፖሊስ በጠየቀኝ መሰረት ታዝቤያለሁ፡፡ ሰነዶች ልናይ ስለሆነ እይልን አሉኝ፡፡ እሺ ብዬ ወደ ቢሮ ገባሁ፡፡ ከቀኑ 8፡00 ይሆናል፡፡ እኛ ከገባን በኋላ ዘላለም ተጠርቶ መጣ፡፡ ላፕቶፑን ራሱ ፓስወርዱን ከፈተው፡፡ ከዚያ ከላፕቶፑ የወጡ ሰነዶች ፕሪንት ተደርገው ፈረምንባቸው፡፡ እንግሊዝኛም አማርኛም ነበር፡፡ ደሞ ምሳ ተጋብዘናል፡፡ ዘላለም ብላ ሲባል አልበላም አለ፡፡ አሁን ሰነዶቹ ምን እንደሆኑ አላውቅም፡፡ ዘላለም የፈረመበት ላይ ነው እኔ የፈረምኩት፡፡ ለማንበብ ግን ጊዜ አልነበረኝም፡፡ ስለዚህ ይዘቱን አላውቀውም፤ እሱ የፈረመበት ስለሆነ ብቻ ፈርሜያለሁ፡፡ አልፈርምም ያለው ሰነድ አልነበረም፡፡ ሌሎች ታዛቢዎችም ነበሩ፡፡ እነሱም ፈርመዋል›› ብለዋል፡፡
ምስክሮች ከመሰማታቸው አስቀድሞ አቃቤ ህግ ባለፈው የተሰጠው ቀጠሮ አጭር በመሆኑ ሌሎቹን ምሰክሮች ለማግኘት ረዘም ያለ ጊዜ ቀጠሮ አንዲሰጠው አንዲሁም አስመዝግቤያለው ካላቸው ሲዲዊች ውስጥ 7ቱ አንዲሰሙለት የጠየቀ ሲሆን የቀሩት ግን ሲዲውን የያዘው ባለሞያ ከአገር ውጪ በመሆኑ ማቅረብ አልቻልንም ብሏል፡፡ የተከሳሾች ጠበቆች ተከሳሾች ከታሰሩ አንድ አመት ሊሞላ ጥቂት አንደቀረ ምስክሮቸን ማዘጋጀት ቀደም ብሎ መሰራት የነበረበት የአቃቤ ህግ ስራ መሆኑን ነገር ግን በተደጋጋሚ እድል እየተሰጠው አንዳልተጠቀመበት በመጥቀስ ዛሬ የቀረቡት የሰው ምስክሮች መጨረሻ አንዲሆኑ እና የቀሩ ማስረጃዎቸን ለመስማት አጭር ቀጠሮ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ “ፍርድ ቤቱ” የአቃቤ ህግን ክርክር በመደገፍ የሚቀጥለውን ቀጠሮ ከአንድ ወር በላይ በማራዘም ግንቦት 18-21 2007 አም ድረስ እንዲሆን አንዲሁም የሲዲ ማስረጃዎቹ በወቅቱ ተሟልተው አንዲቀርቡና ቀሪ ምስክሮቹም በዚያው ቀን ወስኖ ችሎቱ ተጠናቋል፡፡
የዞን9 ማስታወሻ
አንደሁልጊዜው ሁሉ የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ክስ ፓለቲካዊ ነው ያልተሰራ ወንጀል ምስክር አይገኝለትምና ፈጣን ፍትህን የማግኘት መብትን መቀለጃ ላደረገው ፍርድ ቤትም ሆነ የመንግስት ስራ አስፈጻሚ ጓደኞቻችንን ለመፍታት አሁንም ጊዜው አልረፈደም የሚለውን መልእክት ለማስተላለፍ አንወዳለን፡፡

Sunday 5 April 2015

ህወሃት መሪ ያጣ ድርጅት ነው – አበበ ገላው

ህወሃት መሪ ያጣ ድርጅት ነው። እኔ ለህወሃቶች የምመኝላቸው፣ እውነተኛ እራእይ ያለው መሪ እንዲያገኙ ነው።
ለነገ ሳይስቡ ዛሬ ሆድን በኪሳራ ከሞምላት፣ እራስን ከማወደስ፣ ሌሎችን ከማኮሰስ፣ አፈናቅሎ ከመውረስ፣ አምታቶ ከመዝረፍ፣ በሃሰት ከመክሰስ፣ ህዝብን ፈርቶ ከመኖር፣ በደካማ ዜጎች ስቃይ ከመደሰት፣ በዘርና በጎጥ ከመከፋፈል፣ በባዶው ከመጎረር፣ የሃሰት ክብርና ዲግሪ ከጥቁር ገበያ በርካሹ ከመሰብሰብ፣ ጥራት የሌላቸው የሰው አሻንጉሊቶች ከመሰብሰብ የሚያድን መሪ ያስፈልጋቸዋል።
ህወሃቶች ቆራጥ መሪ ሲያገኙ የትናንቱ ስህተታቸው ሁሉ ፍንትው ብሎ ይታያቸዋል። የበደሉትን ሁሉ ይቅርታ ይለምናሉ። አገር ማለት ሁሉም ያልአድርኦ በዜግነቱ ተከብሮ ከማንም ሳይበልጥ ከማንም ሳያንስ ሊኖርበት የሚገባው ምድር መሆኑ ይገለጥላቸዋል። ህወሃቶች መሪ ሲያገኙ ወደ ገደል ቁልቁል ከማብረር ይድናሉ። ፍሬን ይይዛሉ! ቆም ብለው ያስባሉ…
“ውድ የኢትዮጵያ ህዝብ ሆይ! በነጻነት ስም፣ ለችግር፣ ለመከራ፣ ለስደት፣ ለእስራት፣ ለግድያ፣ ለግፍ፣ ለዝርፊያ፣ ለአድልኦ፣ ለስርአት አልባነት፣ ተዘርዝሮ ለማያልቅ በደልና ግፍ ዳርገንሃል። ለሁላችንም የሚሆን አዲስ ምዕራፍ መክፈት ግድ ሆኖብናል። ይቅርታህን እንለምናለን!” የሚል ደፋር መሪ ያሳፈልጋቸዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ሁል ግዜም ይቅር ባይ ነው።
መንደር መሃል እንደነጋበት ጅብ መሄጃ ከማጣቱ በፊት ህወሃት ደፋር መሪ እንዲኖረው እመኝለታለሁ። የእነ መለስን ስህተት ከሚደግም መሪ ይልቅ እወነተኛ ራእይ ያለው ቆራጥ መሪ ያስፈልገዋል። አርቆ አሳቢ፣ ከአድልኦ እና ጠባብነት የጸዳ ከዛሬ ከንቱነት ይልቅ ለመጪው ትውልድ ሁሉ የሚያስብ መሪ..

ወያኔ ጨርቁን ጣለ

 በፕሮፌሰር መስፍን ወ/ማርያም ላይ ጥቃት የተሰነዘረ መሆኑን፤ እሳቸው ይፋ ባደረጉት ጽሁም ላይ ተገልጿል። የደረሰባቸው ጥቃት በዝርዝር ባይገለጽም፤ በፕሮፌሰሩ ማስታወሻ ላይ፤ “ይህን ጥቃት ፈርተን አንሰደድም” የሚል እንደምታ ያዘለ መልእክት ተላልፏል። ለማንኛውም የፕሮፌሰር መስፍንን መልክት ከዚህ በመቀጠል አቅርበነዋል።
mesfin-woldemariam
ዓለም ሁሉ ጠላን፤ በየትም አገር እየሄድን ‹‹የሙጢኝ!›› ከራሳችን መሬት በጉልበት እየተነቀልን፣ ከራሳችን ቤት እየተባረርን፤ ከተወለድንበትና ከአደግንበት አካባቢ እየተፈናቀልን፣ ጭራውን ቆልምሞ እንደሚሮጥ ባለቤቱ እንዳባረረው ውሻ በአገኘነው አቅጣጫ እየሮጥን፣ እጃችንን እያርገበገብን ‹‹የሙጢኝ!›› እንላላን፤ የፈራነውን ሞት በየመንገዱ እናገኘዋለን፤ ሞትን ሸሽተን ሞትን ያጋጥመናል፤ የሞቱ ልዩነት አይታየንም፤ በየመንገዱ የሚያጋጥመው ሞት የውርደት ሞት ነው፤ የብቸኛነት ሞት ነው፤ ዘመድ-ወዳጅ ለቀብር የማይገኝበት ሞት ነው፤ ሠለስት፣ አርባ፣ ሙታመት የማይወጣበት ሞት ነው፤ ባዕድ ምስጥ ያላሳደገውን አካል የሚበላበት ነው፤ የሞት ሞት ነው፡፡
ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ከአገር አስወጥቶ ባዶ መሬት ብቻ ይፈልግ ይመስል የወያኔ ሎሌዎች በማስፈራራት ሁሉም አገሩን እየተወላቸው እንዲሄድ ያቀዱ ይመስላል፤ ጥንት ኢሰመጉ በምሠራበት ጊዜ በየጊዜው በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ሰዎችን በማስፈራራት ሰላማቸውን ለመረበሽ ወደስደት ወይም ወደወንጀል ተግባር የሚመሩ የወያኔ አባለች ነበሩ፤ አሁን እንደገና ብቅ ማለት ጀምረዋል፤ ሕጋዊ ሥርዓት እየላላ ጉልበተኞች በግላቸው ለዘረፋና ለቅሚያ እየተሰማሩ ይመስላል፡፡
ስለራሴ ላውራ፤ ከእኔ የሚፈልጉት ምን እንደሆነ እርግጠኛ አይደለሁም፤ የሚፈልጉት የምኖርበትን አፓርትመንት እንደሆነም አላውቅም፤ በእኔ ቤት ያለ ሀብት የሚባል ለወያኔ አገልጋዮች የሚጠቅም ሁለት የገብረ ክርስቶስ ስዕሎች ብቻ ናቸው፤ (በዚህ አጋጣሚ እነዚህን ስዕሎች ለመግዛት የሚፈልግ ያነጋግረኝ)፤ ከዚህ ሌላ ለወያኔ ዋጋ የሌላቸው መጻሕፍት ናቸው፤ ስለዚህም አሁን በእኔ ላይ የተሰነዘረው ጥቃት እኔን ወደስደት ለመግፋት የሚደረግ ሙከራ ይሆናል፤ በ1992 ግድም ተሞክሮ ነበር፤ አልሠራም፤ ዛሬ ይበልጥ አይሠራም፤ ለማናቸውም ምክንያቱን በትክክል ለማወቅ ባልችልም በእኔ ላይ ዘመቻ መጀመሩን አንድ በቅርብ ከማውቀው ወያኔ በትክክል ተረድቻለሁ፤ ይህንን ዘመቻ በመምራት ላይ ያለውንም ሰው ማንነት ተነግሮኛል፡፡
ይህ አገር የአንድ ጉልበተኛ ቡድን ነው ብዬ አልቀበልም፤ የአባቶቼና የእናቶቼ፣ የኤቶቼና የቅድማያቶቼ አጥንትና ደም የገነባው አገር ነው፤ ማንም ለስደት አይዳርገኝም፤ ማንም አስፈራርቶ ኢትዮጵያዊነት መብቴን መግፈፍ አይችልም፤ አልፈቅድለትም፤ በግልጽ በማያጠራጥር ቋንቋ ኑሮዬም፣ ሕይወቴም፣ ሞቴም እዚሁ ነው፤ ከኢትዮጵያ አፈር የሚለየኝ የለም፡፡
እኔን ለማጥቃት ላሰፈሰፉት ወያኔዎችና ሎሌዎቻቸው አንድ እውነት ልንገራቸው፤– በፈለጉትና በተመቻቸው መንገድ በእኔ ላይ በጉልበታቸው ግፍ ቢፈጽሙ ነገ በነሱ ላይ የባሰ ግፍ እንደሚደርስባቸው ይወቁት፤ ሁልጊዜም ከሕግ የወጣ ጉልበተኛነት ጉልበተኛነትን ያነግሣል፤ በመግደል ድል ይገኛል ብለው የሚያምኑ ወያኔዎች ትንሽ ቆም ብለው ያስቡ፤ በመሞትም ድል ይገኛል፤ በመሞትም ማሸነፍ ይቻላል፡፡
በእኔ ላይ የዘመተው ወያኔ ወይም ሎሌ ማናቸውም ሥራ ውጤት እንዳለው ማወቅ አለበት፤ አንድ ነገር አድርጎ ምንም ዓይነት ውጤት አያስከትልም ብሎ ማሰብ ድንቁርና ነው፤ ይህ የሳይንስ ሕግ ነው።
Ethiopia is the world’s 15th leading imprisoning nation, says ICPS
Posted by The Ethiopia Observatory (TEO)
In officially known prisons in Ethiopia, International Centre for Prison Studies (ICPS) reports that there are 93,044 prisoners. This puts the country into the 15th leading imprisoning nation in the world.
However, since Ethiopia has so many unknown prisons, often where tortures are routinely practised, the number of prisoners in Ethiopia is very small and misleading.
In Africa, even then Ethiopia ranks the second highest imprisoning nation, after South Africa with its 157, 284 prisoners.
At 2.8 percent, however, Ethiopia ranks 31st in the proportion of its female prisoners relative to the total prison population in Africa. The dubious honor in this, i.e., female prisoners rate has gone to the Central African Republic and Rwanda, at 8.2 percent and 6.4 percent, respectively.
At 14.0 percent, Ethiopia ranks 172nd in the world by the number of its pre-trial detainees.
Based on estimated population of 84.2 million in 2011, the prison population rate is 111 in Ethiopia per 100,000 national population. In world prison population rate, Ethiopia is 135th and 19th in Africa. Leading countries in this rates within national populations are Seychelles, Rwanda and South Africa.
Since 2000, according to the ICPS report, prison population in Ethiopia has been increasing significantly. Between the first year and the second, the increase was 12.0 percent and 19.0 percent, it also rising as the total number reached 112,361 in 2010.

Friday 3 April 2015

Ethiopia ranks second poorest country in the world - Oxford University Study

imensional Poverty Index (MPI), published by Oxford University, Ethiopia ranks the second poorest country in the world just ahead of Niger. The study is based on analysis of acute poverty in 108 developing countries around the world. Despite making progress at reducing the percentage of destitute people, Ethiopia is still home to more than 76 million poor people, the fifth largest number in the world after India, China, Bangladesh and Pakistan. India has the world’s largest number of poor people at more than 647 million.

87.3% of Ethiopians are classified as MPI poor, while 58.1% are considered destitute. A person is identified as multidimensionally poor (or ‘MPI poor’) if they are deprived in at least one third of the weighted MPI indicators. The destitute are deprived in at least one-third of the same weighted indicators, The Global MPI uses 10 indicators to measure poverty in three dimensions: education, health and living standards.

In rural Ethiopia 96.3% are poor while in the urban area the percentage of poverty is 46.4%. Comparing the poverty rate by regions, Somali region has the highest poverty rate at 93% followed by Oromiya (91.2%) and Afar (90.9%). Amhara region has 90.1% poverty rate while Tigray has 85.4%.

Addis Ababa has the smallest percentage of poverty at 20% followed by Dire Dawa at 54.9% and Harar (57.9%).

source:Oxford University

Thursday 2 April 2015

መከላከያ ሰራዊት ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ውጥረት መንገሱን የደህንነት ምንጮች ገለጡ
ታህሳስ 17 ቀን 2004 ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የተፈጠረው ውጥረት ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግንባሩ መተካካት እና የብሄር ተዋጽኦን ለማመጣጠን በሚል ሰበብ ከፍተኛ የጦር መኮንኖችን ማባረሩን ተከትሎ የመጣ ነው።
የኢሳት የደህንነት ምንጮች እንደዘገቡት ሰሞኑን 6 ጄኔራሎችና ከ120 በላይ የኮሎኔልነት ማእረግ ያላቸው መኮንኖች ተባረዋል።
የተባረሩት ጄኔራሎች ሁለቱ የትግራይ ፣ 3 የአማራ እና አንድ የኦሮሞ ተወላጅ ናቸው።
በደራሲ ተስፋየ ገብረአብ መጽሀፍ በዳንስ ችሎታው የታወቀው የኦሮሞ ተወላጁ ጄኔራል ባጫ ደበሌም ከተባረሩት ጄኔራሎች መካከል አንዱ ሆኗል።
ከተባረሩት ታዋቂ የትግራይ ጄኔራሎች መካከል በአንድ ወቅት ለመለስ ዜናዊ እጅግ ታማኝ የነበረውና በሁዋላም፣ በታማኝነት ጥያቄ የተነሳ፣ ከጄኔራል ሳሞራ የኑስ ጋር ግጭት ውስጥ የገባው ጄኔራል ዮሀንስ ገብረመስቀል ይገኝበታል።
ከ 3 አመት በፊት የመለስ መንግስት ለጄኔራል ሳሞራ የኑስ የሙሉ ጄኔራልነት፣ ለሙሀመድ ፈረንጂ እና ለአበባው ታደሰ ደግሞ የሊዩተናንት ጄኔራል ማእረግ ሰጥቶ ነበር።
በተመሳሳይ አመትም ሜጀር ጄኔራል ሳእረ መኮንን፣ ሜጄር ጀኔራል ታደሰ ወረደ እና ሜጀር ጄኔራል ባጫ ደበሌ የሊውተናንት ጀኔራል ማእረግ አግኝተዋል።
ብርጋዲየር ጀኔራል ገብራት አየለ ደግሞ ሜጄር ጄኔራል ተብለዋል።
ከአራት አመት በፊት ደግሞ አብረሀ ወልደማሪያም፣ ሞላ ሀይለማርያም፣ አደም ሙሀመድ፣ ገብረእግዚአብሄር መብራቱ፣ ብርሀኑ ጁላ እና ስዩም ሀጎስ ደግሞ የብርጋዴር ጄኔራልነት ማእረግ አግኝተዋል።
በአመቱ ደግሞ ኮሎኔል ክንፈ ዳኘው፣ ገብረሚካኤል ብየነ፣ አከለ አሳየ፣ ህንጻ ወልደጊዮርጊስ፣ ተክለ ብርሀን ካህሳይ፣ ጌታቸው ጊዲና፣ ማሾ በየነ እና ወንዶሰን ተካም እንዲሁ የብርጋዴር ጄኔራልነት ማእረግ ተሰጥቶአቸዋል።
በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ የተፈጠረው ውጥረት በቅርቡ የማእረግ እድገት ያገኙትን መኮንኖች ማእከል ያደረገ በመሆኑ ነው ሲሉ ምንጮች ገልጠዋል።
ቅነሳው በመተካካት ፖሊሲ ላይ የተመሰረተ ነው ከተባለ ከጄኔራል ሳሞራ የኑስ ጀምሮ ያሉት ነባር ጄኔራሎች መቀነስ ነበረባቸው የሚሉት ምንጮች፣ የብሄርን ተዋጽኦ ለመጠበቅ ከሆነም አብዛኞቹ ተባራሪ ጄኔራሎች የትግራይ ተወላጆች በሆኑ ነበር ይላሉ።
እንደምንጮች ዘገባ አሁን ከተባረሩት የትግራይ ጀኔራሎች እና ኮሎኔሎች መካከል አብዛኞቹ ከጄኔራል ሳሞራ የኑስ ጋር ከፍተኛ ቅራኔ ውስጥ ገብተው የነበሩ ናቸው።
የተባረሩት የአማራ ተወላጅ ጄኔራሎች ደግሞ በመፈንቅለ መንግስት መኩራ ተከሰው እስር ቤት የገቡትን የብርጋዴር ጄኔራል ተፈራ ማሞን ሀሳብ ይደግፋሉ ተብለው ክትትል ሲደርገባቸው ቆይቷል።
በመከላከያ ውስጥ የሚታየው ውጥረት ከፍተኛ ደረጃ በመድረሱ የመከላከያ ሚኒስቴር እና አንዳንድ ወታደራዊ ካምፖች በልዩ ሁኔታ እየተጠበቁ ነው።
የተባረሩት ጄኔራሎች እስካሁን ተቃውሞአቸውን በይፋ ወደ አደባባይ አላወጡም።
ይሁን እንጅ በሰራዊቱ ውስጥ ያለው ውጥረት ባልተጠበቀ ሁኔታ በመጨመሩ፣ ጄኔራል ሳሞራ የኑስ ልዩ የክትትል ሀይል መመደባቸውን ለማወቅ ተችሎአል።
በሰራዊቱ ውስጥ የተፈጠረው ውጥረት እስከ ምን ደረጃ ሊሄድ እንደሚችል በሚቀጥሉት ተከታታይ ቀናት ሊታወቅ እንደሚችል ምንጮች ገልጠዋል።
የመከላከያ ሚኒስትር የሆኑት አቶ ሲራጅ ፈርጌሳ የሰራዊቱን የብሄር ተዋጽኦ ለመጠበቅ መንግስት የማመጣጠን ስራ እየሰራ ነው በማለት ለፓርላማ መናገራቸውን ተከትሎ ብሄርንና ታማኝነትን ማእከል ባደረገ መልኩ ቅነሳ እየተካሄደ መሆኑን መዘገባችን ይታወሳል።

Common Struggle.........

Common Struggle for a Common Cause: Afar People’s Party

April 1, 2015
Press Release, March, 31, 2015
The Afar people as a nation and territorial Ethiopian entity plays important role in economic development of the country. Moreover, the region is a significant geo-political and strategic entry point. Nevertheless, the current regime as well as the previous political systems in Ethiopia has seen the Afar people and its region as insignificant political periphery but considers it as a source of exploitation backyard in nation building process.Afar People’s Party (APP) consistently and persistently condemns the killing of innocent tourists.
Afar people are facing multiple challenges of political, economic, social and environmental factors. Most of these issues could be improved and ultimately solved through a just and inclusive political system. However, under the contemporary rule of EPRDF/TPLF regime the magnitudes of these preventable challenges are escalating to the extent that many analysts are predicting the extinction of Afar people as a nation.
The pastoralist are driven from their grazing lands to desert; the territorial clam and land grabbing has been intensified; corruption and bad governance is reigning in Afar region; unemployment rate among Youth is on top of all Ethiopian regions; child and maternal death and other healthcare indicators are the worst in the Horn of Africa; the harassment of federal army and extrajudicial killings are everyday life events; basic democratic values such as political freedom and freedom of expression are stifled and the absolute poverty level is increasing as never seen before. These avoidable challenges as background many Afars who felt marginalisation and injustice are opted to intensify their struggle against the current regime. The purpose of the struggle is to bring about a sustained, democratic and a prosperous Afar Region within democratic Ethiopia.
Historically, the struggle of Afar people has been marred by factors such as regional and tribal factions and lack of clear political objectives. Therefore, the outcome of previous struggle has not landed in a way that secure the future of Afar People. To these problems, a unified struggle is not an option rather a must.
By evaluating the previous failures and recognising the benefit of unified struggle the Afar People Party (APP) has facilitated on 16/02/ 2015 the formation of coalition between the below three groups. The ultimate objective of the common struggle strategy is to forge a common ground for Afar struggle close to the rest of Ethiopian fighting forces for democracy.
ecadf

ኢንጂንየር ይልቃል ጌትነት እንዳይወጡ ታገዱ!!!


ኢንጂንየር ይልቃል ጌትነት እንዳይወጡ ታገዱ በኢትዮጵያ ዋነኛ የሚባለው ተቃዋሚ የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂንየር ይልቃል ጌትነት በአሜሪካ የሚኖሩ የፓርቲውን ደጋፊዎች ለማግኘት እንዳይጓዙ ዛሬ ምሽት በድጋሚ ከቦሌ አለም አቀፍ አየር ማረፊያ ታገዱ።
በእልህና በቁጭት በተለያዩ ሃገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሰማያዊ ፓርቲን ለመደገፍ የሚያደጉት አስተዋጽዎ ከመቸም በላይ እንደሚሆን አገዛዙ ተገንዝቧል። ትግሉ ይቀጥላል !!!