Wednesday, 5 April 2017

‹‹የዐማራ ገበሬዎች ተጋድሎ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ መራዘም ምክንያት ሆኗል›› IRIN

ብራና ሬዲዮ - Branna Radio፤ መቀመጫውን በስዊዘርላንድ ያደረገው የተባበሩት መንግሥታት የተቀናጀ የዜና አውታር (IRIN) በዐማራ ገበሬዎች ተጋድሎ ላይ ሰፋ ያለ ትንታኔ ይዞ ወጥቷል፡፡ የዜና አውታሩ በሰሜን ኢትዮጵያ ያለው የዐማራ ገበሬዎች ተጋድሎ ለአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ አራት ወራት መራዘም ብቸኛ ምክንያት መሆኑን በዝርዝር ያስረዳል፡፡ መጋቢት 3 ቀን 2009 ዓ.ም የታተመው የኢሪን ዘገባ በጎንደርና በባሕር ዳር አስጎብኝ ግለሰቦችን፣ የሃይማኖት አባቶችን፣ የመንግሥት ኃላፊዎችንና የተለያዩ ዜጎችን እንዲሁም በአሜሪካ የተለያዩ ዪንቨርሲቲዎች ተመራማሪዎችንና የኢትዮጵያን ተወላጆች በማነጋገር የሰበሰበው መረጃ እንደሚያመለክተው ገዥው ቡድን በከተማ ያለውን አመጽ የተቆጣጠረው ቢሆንም በገጠር ያለው የዐማራ ታጣቂዎች የእግር እሳት ሆነውበታል ብሏል፡፡ 
የወልቃይት የዐማራ የማንነት ጥያቄ እስካልተመለሰ ድረስ የዐማራ ተጋድሎ ተዋናኝ ገበሬዎች መቼም ቢሆን ትግላቸውን እንደማያቆሙ በየቦታው ያነጋገራቸው ዜጎች በአጽንኦት አስረድተዋል፡፡ ከ20 ሺህ በላይ ወጣቶች ታስረው የስቃይ ሰለባ ቢሆኑም እንዲሁም በብዙ ቦታዎች ያለው አመጽ የቆመ ቢመስልም በሰሜን የዐማራ ገበሬዎች መራር የትጥቅ ትግል ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ እየሄደ ነው ይላል የኢሪን ዘገባ፡፡ 
በነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓ.ም ባሕር ዳር በግፍ ወደ ትግራይ የተወሰደውን የወልቃይትን ሕዝብና መሬት ለማስመለስ ጩኸቱን ያሰማውን የዐማራ ሕዝብ የአገዛዙ ወታደሮች በጥይት ደብድበው ከ52 በላይ ሰዎችን ገደሉ፤ የዐማራ ተጋድሎ በተቀጣጠለባቸው ሳምንታት ብቻ ከ227 በላይ ዜጎች በጥይት ተገደሉ፤ ይህን ተከትሎም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ታወጀ ይላል የዜና አውታሩ ዝርዝር ምልከታ፡፡ 
ይኼው የዜና አውታር በጎንደር ያሉ የሃይማኖት አባቶችንና ግለሰቦችን አናግሮ ‹‹በጎንደር ስለ አርበኛው ጎቤ መልኬና የወልቃይት የዐማራ ማንነት ጥያቄ አስተባባሪው ኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ በፍቅርና በኩራት የማያወራ የለም፤ ገበሬዎች ለማንነታቸው ሕይወታቸውን ከመስጠት ወደ ኋላ አይሉም፤ ዐማራነት ካልተከበረ ወደ ኋላ የሚል የለም›› እንዳሉት በዳሰሳው አስፍሯል፡፡

ሙሉቀን ተስፋው
(ሙሉ የዜና አውታሩን ዘገባ ለመመልከት ከዚህ ቀጥሎ ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑት
http://www.irinnews.org/analysis/2017/04/03/ethiopia-extends-emergency-old-antagonisms-fester

Tuesday, 4 April 2017

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር ስም እየተራቆተ መሆኑ ተገለጸ

ኢሳት (መጋቢት 26 ፥ 2009)

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንደ ሃገሪቱ ልማት ባንክ በብድር ስም እየተራቆተ መሆኑን ምንጮች ገለጹ። ለባንኩ ፕሬዚደንት በጉቦ መልክ እጅግ ዘመናዊ ቤት የተሰራላቸው ቢሆንም፣ እርሳቸው የሚኖሩበት ግን ባንኩ በዋስትና በወረሰው ቤት ውስጥ መሆኑንም መረዳት ተችሏል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክና የኢትዮጵያ ልማት ባንክ የህወሃት ንብረት ለሆነው ኤፈርት ኩባንያዎች ብድር ምንጭነት በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት፣ ከገዢው ፓርቲ ጋር ቅርበት ያላቸው ባለሃብቶችም ከህግና ደንብ ውጭ ከፍተኛ ገንዘብ እየወሰዱ ሲሆን፣ የአንዳንዶቹ ብድር ከ2 ቢሊዮን ብር መብለጡንም ለኢሳት በዝርዝር የደረሰው መረጃ ያስረዳል።

በዚሁ ረገድ በግንባር ቀደምትነት ከሚጠቀሱት አንዱ የተክለብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽን ባለቤት አቶ ተክለብርሃን አምባዬ መሆናቸውም ተመልክቷል። ባለሃብቱ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወሰዱትና ያልተመለሰው ብድር 1.5 ቢሊዮን ብር የደረሰ ቢሆንም፣ ዕዳቸውን ሳይከፍሉ ያለጨረታ ግዙፍ የባንኩን ፕሮጄክቶች እየወሰዱ ይገኛል።

መገናኛ አደባባይ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ህንጻ ያለጨረታ መስራታቸውን የሚገልፁት የባንኩ ምንጮች፣ ባንኩ ልደታ አካባቢ የሚያሰራውንም ህንጻ በተለየ ሁኔታ ያለጨረታ እንዲወስዱ መደረጉም ተመልክቷል። ጨረታውን ያሸነፈው ድርጅት ተገልሎ ግንባታው ለተክለብርሃን አምባዬ ኮንስትራክሽ የተሰጠበት ሁኔታ በግልፅ አልተመለከተም።

የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ህወሃት አመራሮች እንዲሁም ቀደምት ታጋዮችና የጦር አዛጆች በይበልጥም ከአቶ አባይ ጸሃዬና ከብ/ጄኔራል ክንፈ ዳኘው ጋር በቅርበትና በሽርክና ይሰራሉ የሚባሉት አቶ ተክለብርሃን አምባዬ፣ በአቶ አባይ ጸሃዬ ትዕዛዝ ይንቀሳቀሳሉ ለሚባሉት የባንኩ ፕሬዚደንት አቶ በቃሉ ዘለቀ ዘመናዊ መኖሪያ ቤት ገንብተው በስጦታ መስጠታቸውን መረዳት ተችሏል።

አቶ በቃሉ ዘለቀ በስጦታ የተበረከተላቸው ቤት በዋስትና አስይዘው ራሳቸው ብድር እንደወሰዱ የሚገልጹት ምንጮች፣ አዲሱን ቤት አከራይተው ባንኩ በዋስትና በወረሰው ቤት ውስጥ እንደሚኖሩ ገልጸዋል። ባንኩ በ10 ሚሊዮን ብድር በዋስትና ይዞ የወረሰውን ቤት ባንኩ ሽጦ ገቢ ማድረግ ሲገባው፣ የባንኩ ፕሬዚደንት እንዲኖሩበት መደረጉ ጥያቄ ማስነሳቱን መረዳት ተችሏል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የቦርድ ሊቀመንበርነትን በአሁኑ ወቅት የያዙት አቶ በረከት ስምዖን ቢሆኑም፣ በእያንዳንዱ የባንኩ እንቅስቃሴ የባንኩን ፕሬዚደንት አቶ በቃሉ ዘለቀን እየተቆጣጠሩ የፈቀዱትን የሚያስፈጽሙት የባንኩ የቦርድ ሊቀመንበር አቶ አባይ ጸሃዬ መሆናቸውንም የኢሳት ምንጮች ገልጸዋል።

አቶ አባይ ጸሃዬ አሁን የቦርድ ሊቀመንበርነቱን ቢለቁም፣ የቦርድ አባል መሆናቸው ታውቋል።

Thursday, 23 March 2017

Ethiopia: Political prisoner exposes horrific torture in prison

Habtamu Ayalew

ESAT News (March 23, 2017)

A former political prisoner says TPLF investigators inflict unimaginable physical and psychological torture on prisoners including but not limited to damaging their reproductive organs and making them sterile for life.

In an interview with the VOA Amharic service, Habtamu Ayalew, former spokesperson for the opposition Andinet Party said not only he had endured physical torture, the psychological scar is still enduring even worse.

Habtamu said what the investigators inflict on prisoners is something he wouldn’t dare to say in public due to it’s graphic nature and that his religion would allow him to speak about the bestial acts of regime investigators.

He said investigators would hang a bottle of water on prisoners’ genitals while the prisoners are hanged on a pole to obtain forced confession. “They also tie ropes to your genital and pull it for a period of time,” he told the VOA. “I know so many prisoners who have become sterile due to this heinous torture.”

He said prisoners at the Central Investigation Bureau in Addis Ababa,   widely considered as Ethiopia’s torture chamber, are only allowed to use the bathroom twice a day for an average of 2 min at a time.

Habtamu recounted his experience at the Investigation Bureau where he was once put in solitary confinement without access to a bathroom and was forced to use plastic bags and water bottles. “They would also punch you on the back, right where your kidneys are, so you will take a leak on yourself. They would tie prisoners to a chair for days on till they defecate on themselves.”

Habtamu mentioned by name some of the political prisoners that have undergone through some of the despicable acts of torture: Abebe Wergesa, Lejisa Alemayehu, Angaw Tegegn, Agbaw Setegn, Engidaw Wanaw and Abay Zewdu.

Security forces arrested Habtamu Ayalew and detained him for over two years falsely accusing him of having links to Patriotic Ginbot 7, an armed group fighting the tyrannical regime for a democratic change. He was later released and came to the United States to get medical attention to a serious ailment that resulted from the torture he had endured at prison.

Saturday, 31 December 2016

በውጭ ብድር የተጀመሩ የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታቸው ሳይጠናቀቅ የብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ


ኢትዮጵያን ስኳር ላኪ ሃገር ያደርጋሉ ተብለው ከውጭ በተገኘ ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ግንባታቸው ከሰባት አመት በፊት የተጀመሩ ፋብሪካዎች ግንባታቸው ተስተጓጉሎ እያለ ብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ።

በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ውስጥ የሚገኘው መንግስት በበኩሉ በመገንባት ላይ ያሉትን ጨምሮ በስራ ላይ ያሉ የስኳር ፋብሪካዎች ከውጭ ባለሃብቶች ጋር በሽርክና ለመስራው መወሰኑን ይፋ አድርጓል።

መንግስት ከተለያዩ አበዳሪ የፋይናንስ ተቋማት በብድር ባገኘው ገንዘብ የወልቃይት፣ የኦሞ፣ ኩራዝ አንድ ሁለትና ሶስት እንዲሁም የጣና በለስ ቁጥር አንድና ሁለት ፕሮጄክቶችን ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወሳል።

ይሁንና ሃገሪቱን ከስኳር እጥረት በማላቀቅ ኢትዮጵያ ምርቷን ወደ ውጭ ሃገር በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እንድታገኝ ያደርጋሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸው ፋብሪካዎች አብዛኞቹ በጅምር ላይ መቅረታቸው ተመልክቷል።

ፋብሪካዎቹ በከፍተኛ የፋይናንስ እጥረት ውስጥ በመግባታቸውና የተጀመሩ ፕሮጄክቶችን ለማስጨርስ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ በማስፈለጉ ምክንያት መንግስት ነባሮቹንና አዳዲስ ግንባታዎች በሽርክና ለማካሄድ መወሰኑን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ፋብሪካዎቹ በአምስት አመት ውስጥ ወደ ምርት ይገባሉ ተብሎ የተጠበቁ ሲሆን፣ ግንባታቸው በ25 በመቶ ላይ የሚገኝ እንዳለም የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን መረጃ ያመለክታል።

ፋብሪካዎች ለሰባት አመት ያህል መጠናቀቅ ባለመቻላቸው ከአበዳሪ ካላት የተገኘ ብድር የመጀመሪያ ክፍያ የመጀመሪያ ጊዜው መቃረቡን ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል።

የኮንትራት አስተዳደርና የፋይናንስ ችግሮች ፋብሪካዎቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዳይጠናቀቁ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል ዋነኞቹ መሆናቸውን የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ሃላፊ የሆኑት አቶ ጋሻው አይችሉህም ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል።

በሃሙስ ዘገባችን ለጣና በለስ የስኳር ፋብሪካ ተዘጋጅቶ የነበረ የሸንኮራ አገዳ ምርት ፋብሪካው ባለመጠናቀቁ ምክንያት ምርቱ እንዲቃጠል መደረጉን መዘገባችን ይታወሳል።

ከፋብሪካው በፊት ለምርት ደርሶ የነበረው የሸንኮራ አገዳ እንዲወገድ የተወሰነው ምርት ከፍተኛ ገንዘብ የፈሰሰበት እንደነበር ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት ይገልጻሉ።

በሃገሪቱ ያሉ ጅምርና ነባር የስኳር ፋብሪካዎችን ከውጭ ባለሃብቶች ጋር በሽርክና ለማስተዳደር የቻይንና የአውሮፓ ሃገራት በመደራደር ላይ ሲሆን፣ መንግስት ያጋጠመው የፋይናንስ እጥረት ወደዚህ አማራጭ እንዲገባ ማስገደዱንም ባለሙያዎች አስተድተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የጣና በለስ አንድና ሁለት የስኳር ፕሮጄክቶችን ለአንድ የቱርክ ኩባንያ 75 በመቶ ድርሻን ለመስጠት ሲካሄድ የነበረ ድርድር መቋረጡም ታውቋል።

በዲሳ ግሩፕ የተሰኘ ይኸው የቱርክ ኩባንያ ወደ አንድ ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ገንዘብ በመመደብ የፕሮጄክቱን 75 በመቶ ባለቤትነት ለመረከብ ድርድር ጀምሮ የነበረ ሲሆን፣ ከገንዘብ አከፋፈልና ከትርፉ ክፍፍል ጋር ከመንግስት ጋር ሊደርስ አለመቻሉ ተገልጿል።

ይሁንና ሁለቱም ወገኖች ተፈጥሯል በተባለው አለመግባባት ዙሪያ ዝርዝር መረጃን ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ኢሳት

Tuesday, 22 November 2016

አንድ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በትግራይ ተወላጅ ተማሪ ዘግናኝ ጥቃት ተፈፀመበት

አንድ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በትግራይ ተወላጅ ተማሪ ዘግናኝ ጥቃት ተፈፀመበት።
በተመሳሳይ ህዳር 21 ያልተጠበቀ ጥቃት ሊፈፅሙ መዘጋጀታቸውን በቅርብ የሚከታተሏቸው ተማሪዎች መረጃውን አውጥተውታል።
የትግራይ ተውላጅ ተማሪዎች ሌሎች ተማሪዎችን መተንኮል ጀምረዋል።በተለይ በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ ተደጋጋሚ ትንኮሳዎችን አድርገዋል። ከነዚህም መካከል አክሊሉ መንገሻ የተባለ የ3ኛ አመት ማኔጅመት ተማሪ ትናንት ምሽት ጆሮውን_ቆርጠውታል፤ ልጁም ለህክምና ወደ አዲስ አበባ ተልኳል፤ወንጀል ፈፃሚውም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል ተብላል።
ቆራጩ ትግሬ ሲሆን አክሊሉ ግን የአቦምሳ (ናዝሬት አካባቢ) ልጅነው ፡፡ ልጁ ለህክምና  ወደ አዲስ አበባትናንት የተላከ ሲሆን የኢትዮ ስታር ሆቴል ባለቤት(ትግሬ )  ለማደራደር በሽምግልና ቢመጡም አልተሳካም።ሌላ ደግሞ የአደት ልጅ 3ኛ አመት ማርኬትንግ ተማሪም እንድሁ ጥቃት ሊያደርሱበት ሞክረው ሳይሳካላቸው ቀርቷል ፡፡ በተለይ ትናንትና ዛሬ ብዙ ተማሪዎችን ሲተናኮሉና ሲደባደቡ ነበር።
በዚህ አጋጣሚ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እርስበርሳችሁም ሆነ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጋር አፋጣኝ መረጃ ትለዋወጡ ዘንድ እንመክራለን።

Sunday, 16 October 2016

ሰበር_መረጃ አስቸኳይ የፋይናንስ አዋጅ ሊታወጅ እንደሆነ ተሰማ

ሰበር_መረጃ….አስቸኳይ የፋይናንስ አዋጅ ሊታወጅ እንደሆነ ተሰማየብሔራዊ ባንክ ውጭ ምንዛሪ ካዝና ባዶ ነው

October 16, 2016

የኢህአዴግ ጽ/ቤት በትርምስና የእርስ በእርስ ውንጀላ ላይ ነው። በውጪ እና በሀገር ውስጥ ኢንቬስተሮች ከኤክስፖርት ይገኝ የነበረው የውጭ ምንዛሪ በ5 ወራት ውስጥ በ71.1 በመቶ በመቀነሱ ለመጀመሪያ ጊዜ የ1.9 ቢሊዮን ዶላር የገቢ ውድቀት ታይቷል። ከተጠበቀው በታች በመቀነሱ ይሄንን የህዝብ አገልግሎት ሰጪ የሆኑ የትምህርት ቤት በጀት (የመምህራን ደሞዝን ጨምሮ)፣ የጤና አገልግሎት፣ ትራንስፖርት፣ ከፍተና ወጪ ያስከተለው የፖሊስ ሰራዊትና የወታደሮች ደሞዝ በዚህ የበጀት ቀውስ ምክንያት በመስተጓጎሉ አዲስ አዋጅ ማስፈለጉ ተሰምቷል።

ከሁሉም አስከፊ የሆነው ከቻይና ሌሎች አበዳሪዎች ለኢንቨስትመንስት ጉዳይ ተብሎ የተገኘው ብድር 16 ቢሊዮን ዶላር በመድረሱ በመጀመሪያው የክፍያ በ2016 አመት አስከፊ የፋይናንስ ቀውስ መገባቱ ምክንያት ሆኗል። ኢትዮጵያ በአሳሳቢ የዕዳ ሽክም ከአለም 11ኛ ሆናለች። ከዚህ ባለፈ ለውድቀቱ ተጨማሪ ምክንያት የሆነው እርዳታ ሰጪ ሀገሮች በየጊዜው የሚያስገኙት የበጀት ድጋፍ እየቀነሰ በመምጣትና ወደ ሰብዓዊ አስቸኳይ የምግብ ርዳታ ላይ ትኩረት በማድረጋቸው መሆኑም ጭምር ነው።
http://www.satenaw.com/amharic/archives/23331

Monday, 3 October 2016

የኢሬቻ በዓል ጭፍጨፋ

ፕሮፌሰር መስፉን ወ/ማሪያም
የኢሬቻ በዓል ጭፍጨፋ፡--- እንደሰው ያሳዝነኛል፤ ያሳፍረኛል፤ እንደኢትዮጵያዊ ዜጋ ያዋርደኛል፤ ያሳጣኛል፤ አለኝ የምለውን የጨዋነት ባህል፣ ይሉኝታና ክርስስቲያናዊ ሰብአዊነት ያጎድፍብኛል፤ ራቁቴን በዓለም ሕዝብ ፊት ያቆመኝ ይመስለኛል፡፡
ለሥልጣን ብዙ ሰዎች ሰዎችን አጫርሰዋል፤ ብዙ ንብረትን አውድመዋል፤ የብዙ ሕዝቦችን የእድገት እርምጃ አግደዋል፤ ወደኋላም መልሰዋል፤ ሞት እየቀጠፋቸው ሥልጣናቸው ባልወደዱት እጅ ገብቷል፡፡
ለሀብት ብዙ ሰዎች ሰዎችን አጫርሰዋል፤ ከሰው ልጅ ሕይወት፣ ከሰው ልጅ ምቾት ሀብት በልጦባቸው ጤንነታቸውን እያጡ በማያሸንፉት ሞት ተቀጥፈዋል፤ ከሰው ልጅ የበለጠባቸው ሀብት እንኳን ለነሱ ለልጆቻቸውም ሳይሆን ተዝረክርኮ ቀርቷል፡፡
የባለሥልጣንና የሀብታሞች ሎሌ በመሆን ወንድም ወንድሙንና እኅቱን ገድሎ፣ ጎረቤቶቹንና ወገኖቹን አስቀይሞ ከውርደት ኑሮ በቀር ክብርንና ኩራትን አያገኝም፤ የሠራውን ሥራ፣ ወንድሙን ወይም እኅቱን መግደሉን፣ ከእሱ በቀር የሚያውቀው የለም ይሆናል፤ ይህ አእምሮውም ውስጥ ልቡም ውስጥ የተለጠፈ እውቀት በመቃብርም ሆነ ከመቀብር ውጭ አይለየውም፤ ማናቸውንም ምቾት ይነሳዋል፡፡
መግደልም ሆነ ማስገደል የመጨረሻው የውድቀትና የጻዕር ምልክት ነው፤ ወይም የታቀደ የመጨረሻው እልቂት መጀመሪያ ነው፤ የተጠቂው ወገን ሲመርረው አጥቂው ካልጎመዘዘው፣ አጥቂው እስቲጎመዝዘው ድረስ የተጠቂው ምሬት ቋቅ እስቲለው ይቀጥላል፤ የተጠቂው ምሬት ቋቅ የሚያስደርግ ደረጃ ላይ ሲደርስ የአጥቂውም መጎምዘዝ ወደምሬት ያሸጋገራል፤ ትእግስት የጎደለው የአጥቂ ጉልበተኛ ምሬትና ቋቅ የሚል የተጠቂ ምሬት ሲጋጠሙ ውጤቱ እልቂት ነው፤ ጉልበተኛ ጉልበቱ እስቲሰበር የሞተ ኅሊና (እንጉርጉሮ ወይም አሁንም እንጉርጉሮ) በሚለው ግጥሜ በከፊል የሚከተለውን ብዬ ነበር፡---
ከሳሽ፣ ተከሳሽ፣ ዳኛ መሆን
እንዴት ይችላል መበየን?
ሲፍነው ግን ኅሊናውን፣
አይለይም ጨለማውን ከብርሃን!
ኅሊናውን የገደለ ሰው
ማን ሊቀረው? ምን ሊያቅተው?
የጉልበቱ መሣሪያ ነው፤
ጊዜ ጉልበቱን እስቲሰብረው!
እግዚአብሔር ከመጨካከን ፉክክር ይጠብቀን፡፡