Tuesday 13 March 2018

የአግ7 አርበኞች ነዳጅ በጫነ የህወሓት መከላከያ ተሽከርካሪ ላይ ጥቃት ፈፀሙ

መጋቢት 03 ቀን 2010 ዓ/ም ከሱዳን ካርቱም ለህወሓት ገዳይ አጋዚ ጦር አገልግሎት የሚውል ነዳጅ የጫነ ተሽከርካሪ በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ዞን ደበጫ እንዳለፈ አማኑኤል ከተማ መግቢያ ላይ የአግ7 አርበኞች በደፈጣ በወሰድት እርምጃ ነዳጅ የጫነው ቦቴ ከነ ተሳቢው ሙሉ በሙሉ ጋይታል ፡፡ ይህ ከባድ ቦቴ መኪና ከነ ተሳቢው በጠቅላላ 44,000(አርባ አራት ሽህ ) ሌትር ቤንዝል ጭኖ የነበረ ሲሆን ተሽከርካሪውም ከነ ነዳጅ ሙሉ በሙሉ ተቃጥላል ፡፡ ህወሓት በአሁኑ ሳዓት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ በማወጅ ኑፁሀንን በጠራራ ፀሀይ በግፍ እየጨፈጨፈ በሚገኝበት ወቅት ለዚህ እኩይ ስራው ዋና ጉልበቱ ነዳጅ በመሆኑ በዚህ ላይ በተጠና መንገድ ዘመቻው የተከናወነ መሆኑን የአግ7 መረጃ ክፍል ገልፃል ፡፡ በመሆኑም ይህ እና ሊሎች መሰል እርምጃዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ እየገለፅን ማንኛውም ለዚህ ዘረኛ ስርዓት አገልገሎት በሚውሉ ንብረቶች ላይ በተጠናከረ ፣ንገድ እርምጃው ይቀጥላል ፡፡ በዚህ ዘመቻ የተሳተፋ የአግ7 አርበኞች በሰላም ወደ ቦታቸው ተመልሰዋል ፡፡ ድል ለሕዝብ !!! የአግ7 ዘመቻ ነፃ ትውልድ ፡፡ 

No comments:

Post a Comment