ወይ ይች ሀገር!!
ሼህ መሀመድ ሁሴን አል አሙዲን ለክሊንተን ፋውንዴሽን በ2006 ዓመተ ምህረት 20 ሚሊዮን ዶላር መስጠታቸውን ፒተር ስዋይዘር የተባሉ ጸሀፊ በቅርቡ ለህተመት በሚያበቁት መጽሀፋቸው ላይ በይፋ አጋልጠዋል። (እንኳን 20 ለምን 200 ሚሊዮን ዶላር አይሰጣቸውም? ብለን ዝም እንዳንል፤ ስጦታው የተሰጠው በኢትዮጵያ መንግስት ስም መሆኑ ያማል።ይህንንም አል አሙዲ -ለፋውንዴሽኑ በጻፉት ደብዳቤ አረጋግጠዋል። ለምን በኢትዮጵያ መንግስት ስም ሰጡ? የስጦታው ምክንያት ምንድነው?የሚል ጥያቄ ከተነሳ፤ አል አሙዲ በዚያው በስጦታ ደብዳቤያቸው ላይ ፦የቡሽ አስተዳደር የውጪ ጉዳይ ፖሊሲ-በክሊንተን ጊዜም ሳይቀየር እንዲቀጥል መማጸናቸው(መጠየቃቸው)ተመልክቷል።
ያንንም ተከትሎ በባለቤታቸው ስም ገንዘቡን የተቀበሉት የወቅቱ የአሜሪካ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ሄላሪ ክሊንተን የአሜሪካ መንግስት በኢህአዴግ ላይ ማእቀብ እንዲጣል ያረቀቀው አዋጅ እንዲሰረዝ ፣ ይልቁንም አሜሪካ ለኢህአዴግ አስፈላጊውን እርዳታ እንድትሰጥ ማስደረጋቸውን ደራሲው አጋልጠዋል።
(እየተዛቀ የሚወጣው የሻኪሶ (የሀገሬ)ወርቅ፤ ሀገሬን ለማፈን እንደሚውል መስማት እንዴት ያማል!!!)
“ኢህአዴግ እንድሆን ያጠመቀኝ አሰፋ ማሞ ነው” አል-አሙዲለማንኛውም ይህ የአል አሙዲን እና የክሊንተን ጉዳይ በፎክስ ኒውስ ሰፊ ሽፋን ያገኘ ወቅታዊ አጀንዳ ሆኗል። ሊንኩ ከታች አለ፤ ያዳምጡት፦ አረዳው ፎክስ ኒውስ ትልቅ አጀንዳ ነው የሰጠህ። ለጊዜው እገሊትና እገሌን ተዋቸውና ይህን ጉዳይ ተወያይበት፣ተነጋገርበት..ከዚህ (ከሀገር)የሚበልጥ አጀንዳ የለም።
http://www.realclearpolitics.com/…/fox_news_special_the_tan…
Wednesday, 29 April 2015

- ሙሉ ልብሴን እንዳወልቅ ተገድጄ ራቄቴን በወንድ መርማሪዎች ፊት ስፓርት አንድሰራ እገደድ ነበር ፡፡ “ሴትነትሽ አንዲህ ከሚዋረድ አመጽ እንዳነሳሳሽ እመኚ ተብያሁ”
- በሌሊት ግርፋት የሚፈጸምበት ክፍል ውስጥ ገብቼ ጫማሽን አውልቂ ተብዬ ጫማዬን አውልቄ ከቆምኩ በኋላ ውስጥ እግርሽን ከምትገረፊ አመጽ ማነሳሳትሽን አምነሽ ፈርሚ ተብያለሁ፡፡
- ሰጠሁት የተባለው ቃል ሰዎች በሚቀጥለው ክፍል እየተደበደቡ የጩኀት ድምጻቸው እየተሰማ ፈርሚ ተብዬ የተባልኩት ቦታ ላይ ሳላነብ በፍርሃት ፈርሜያለሁ።
- በተለያዬ ምርመራ ወቅቶች "ለነጭ አገሪትዋን የሸጥሽ ሸርሙጣ ውሻ ባንዳ..." አንዲሁም ለመጸፍ የሚከብዱ አፀያፈ ስድቦች በየቀኑ እሰደብ ነበር ፡፡
(*ይህ ጽሁፍ ለኢትዬጲያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን ከገባው አቤቱታ ተቀንጭቦ የተወሰደ ነው)
Saturday, 25 April 2015
Anniversary of Arrest of Ethiopia’s Journalists
US State Dept. on Anniversary of Arrest of Ethiopia’s Journalists
April 24, 2015
STATEMENT BY MARIE HARF, ACTING SPOKESPERSON
Anniversary of the Arrest of Ethiopia’s Zone 9 Bloggers and Three Journalists
Tomorrow, April 25, marks one year since Ethiopia arrested six Zone 9 bloggers and three other journalists. These nine individuals—Befekadu Hailu, Zelalem Kibret, Atnaf Berhane, Natnael Feleke, Mahlet Fantahun, Abel Wabella, Asmamaw Hailegiorgis, Edom Kassaye, and Tesfalem Waldeyes—joined 10 other journalists already imprisoned in Ethiopia, bringing the total number of jailed journalists in Ethiopia to 19, including two Eritrean nationals. This is more than any other country in Africa. In July 2014, Ethiopian authorities charged the six bloggers and three journalists with terrorism under its Anti-Terrorism Proclamation. Their trial is ongoing. Ethiopia also charged one other Zone 9 blogger—Soliyana Shimelis—who was out of the country when her colleagues were arrested, with terrorism, in absentia. Soliyana has been unable to return to Ethiopia and, along with dozens of other Ethiopian journalists, now lives in exile.
Restrictions on press freedoms are inconsistent with the rights outlined in the Ethiopian constitution. Space for media, civil society organizations, and independent voices and views are crucial for democratic progress, development, and economic growth. While we recognize a judicial process is underway, we urge the Ethiopian Government to release journalists and other individuals imprisoned for exercising their right to freedom of expression, particularly those imprisoned who may merit humanitarian release on medical grounds. We urge Ethiopia to refrain from using its Anti-Terrorism Proclamation as a mechanism to curb the free exchange of ideas.
http://ecadforum.com/2015/04/24/us-state-dept-on-anniversary-of-arrest-of-ethiopias-journalists/
Friday, 24 April 2015
ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው
” ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው Professor Berhanu Nega
የአርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያቀረቡት አስቸኳይ ጥሪ
የተከበራችሁ ወገኖቼ፤ ከሰላሳ በላይ የሆኑ ወገኖቻችን አይ ሲስ በተሰኘ ህሊና ቢስ፣ ፀረ-ሰው እና ፀረ-ስልጣኔ ቡድን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ የመገደላቸው መርዶ ከትናንት ወዲያ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓም ደርሶን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት በመሪር ሀዘን ውስጥ ነን። ዛሬ “እግዜር ያጥናህ” ወይም “እግዜር ያጥናሽ” የሚባል ሰው የለም። ሁላችንም ሀዘንተኞች ነን። ካጣናቸው ቁጥራቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ወገኖቻችን አሁንም በአራዶች መዳፍ ውስጥ መሆናቸው ሀዘናችን እጅግ የበረታ ያደረገዋል። ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ሆኖም በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ሊቢያ ውስጥ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሁንም ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ናቸው። ሌሎች በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ደግሞ በየመን ከሰማይም ከምድርም በቦንብና በጥይት እየተማገዱ ነው።
ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች ስብዕናችንን ገፈፉን።
የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?
በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው። እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።
ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።
ወገኔ፤ ዛሬ ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤ እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።
የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።
ብርሀኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር
ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም
የተከበራችሁ ወገኖቼ፤ ከሰላሳ በላይ የሆኑ ወገኖቻችን አይ ሲስ በተሰኘ ህሊና ቢስ፣ ፀረ-ሰው እና ፀረ-ስልጣኔ ቡድን በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ የመገደላቸው መርዶ ከትናንት ወዲያ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓም ደርሶን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት በመሪር ሀዘን ውስጥ ነን። ዛሬ “እግዜር ያጥናህ” ወይም “እግዜር ያጥናሽ” የሚባል ሰው የለም። ሁላችንም ሀዘንተኞች ነን። ካጣናቸው ቁጥራቸው በብዙ እጥፍ የሚበልጥ ወገኖቻችን አሁንም በአራዶች መዳፍ ውስጥ መሆናቸው ሀዘናችን እጅግ የበረታ ያደረገዋል። ቁጥራቸው በትክክል የማይታወቅ ሆኖም በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያዊያን ዛሬም ሊቢያ ውስጥ ናቸው። በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሁንም ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ናቸው። ሌሎች በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ደግሞ በየመን ከሰማይም ከምድርም በቦንብና በጥይት እየተማገዱ ነው።
ለምንድነው ኢትዮጵያዊያን እንዲህ እሳት ውስጥ ለመማገድ የምንደፍረው? መልሱ ግልጽ ነው። አገር ውስጥ ተስፋ የለም፤ ወያኔዎች ተስፋችንን አጨለሙት። ከሳዉዲ በመከራ የተመለሱ ወንድሞቻችን ናቸው በሊቢያ በኩል ለመሰደድ ሲሞክሩ በአይ ሲስ ተይዘው የታረዱት። ወያኔዎች አገራችንና ክብራችን ዘረፉን። ወያኔዎች ስብዕናችንን ገፈፉን።
የዘመኑ ጥቂት የህወሓት ቱጃሮች ፎቆችን እየገነቡ በነሱ መጥገብ እኛ እንድናገሳላቸው ይፈልጋሉ። የኢትዮጵያ ሕዝብ መራቡ፣ መታረዙ፣ መደህየቱ እውነት ነው፤ ሆኖም ግን “ተራብኩ”፣ “ታረዝኩ”፣ “ደኸየሁ” ብሎ መናገር አይችልም። እውነት መናገር ያስቀጣል፣ ያስወነጅላል። በፍርደ ገምድል ችሎት እውነት መናገር “ሽብርተኛ” ያስብላል። እስር ቤቶችን የተሞሉት ለእውነት፣ ለፍትህ፣ ለነፃናትና ለእኩልነት በቆሙ ሰዎች አይደለምን?
በአይ ሲስ ያሳረደን ማነው? መልሱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ ነው። ያዋረደን፣ በአይ ሲስ ቢላዋ ያሳረደን ህወሓት ነው። እንደ አገርና እንደ ሕዝብ የደረሰብን ውርደት የትም ብንሄድ የምናመልጠው አልሆነም። በአገር ውስጥ የደረሰብንን ውርደት ለማምለጥ ስንሰደድ ውርደት ተከትሎን ይመጣል።
ወገኖቼ፤ ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ከኢትዮጵያ የተሻለች አገር ሊኖረን አይችልም። ዛሬ የመሸሻ ጊዜ አይደለም። አገራችንን ከወያኔ ነጥቀን፤ በአገራችን ኮርተን በሰላም መኖር እንሻለን። ይህ መብታችን ነው። አገራችን የኛ ነች። አገራችን የጥቂት ወያኔዎች መፈንጫ አይደለችም።
ወገኔ፤ ዛሬ ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም በአርበኖች ግንቦት 7 ስም የማደርግልህ ጥሪ አድምጠኝ። በሀይማኖት፣ በብሔር፣ በጾታ ልዩነት ሳታደርግ ዛሬ በአንድነት እንደተሳህ አንድነትህን እንደጠበቅህ ቀጥል። አንድነትህን ለመሸርሸር ወያኔ የማይፈነቅለው ድንጋይ አይኖርም፤ ለወያኔ ዱለታ ጆሮህን አትስጥ። የወያኔ አገዛዝ እንዲያበቃ በአንድነት ተነስ። ዛሬ የጀመርከው ትግል እዳር ሳይደርስ እረፍት የለንም።
አርበኞች ግንቦት 7፣ ከትግራይ፣ ከኦሮሚያ፣ ከአፋር፣ ከኦጋዴን፣ ከጋምቤላ፣ ከቤሻንጉል ድርጅቶች ጋር በመጣመር የአገር አድን ኃይል የመገንባት ሥራውን እያጠናቀቀ ነው። እኛ ልጆችህ በብሔርም ሆነ በሀይማኖት ሳንከፋፈል፤ ከትግራይ እስከ ኦጋዴን፤ ከአፋር እስከ ጋምቤላ ሁሉንም የኢትዮጵያ ማኅበረሰብ ባካተተ ስብስብ ውስጥ አብረን ህወሓትን እየታገልን ነው። ይህ ትግል ግን የአንተ የኢትዮጵያ ሕዝብ ትግል ነው። የትግሉም የአገሪቷም ባለቤት አንተ ነህ። ስለሆነም ተነስ! “እንቢኝ” በል። ዘርፈ ብዙ የትግል ስልቶችን በመጠቀም ወያኔን አዳክም። የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ! በትግልህ ፍሬ የአገርህ ባለቤት ሁን።
የመከላከያና የፓሊስ ሠራዊት አባላት ሆይ!እናንተ የሕዝብ አካላት ናችሁ። የደረሰብንን ብሔራዊ ውርደት እያያችሁ፤ እሮሮዓችን እየሰማችሁ በሕዝብ ላይ መተኮስ በራሳችሁ ጭንቅላት ላይ መተኮስ ማለት መሆኑን ለደቂቃ እንኳን አትዘንጉ። ይልቁኑ ዛሬውኑ ነፃነትና ፍትህ ከጠማው ወገናችሁ ጎን ቁሙ።
የኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የወጣትነት የፈጠራ ችሎቻችሁ መፈተኛው አሁን ነው። ለእያንዳንዱ ጥቃቅን ጉዳይ መመሪያ እስኪሰጣችሁ አትጠብቁ። እያሰላችሁ፣ እያጠናችሁ፣ እያደባችሁ፣ ወያኔን ታገሉ።
የታፈረች፣ የተከበረችና የበለፀገች ኢትዮጵያን እውን እናደርጋለን።
ብርሀኑ ነጋ
የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ ሊቀመንበር
ሚያዝያ 13 ቀን 2007 ዓም
Thursday, 16 April 2015
እስከመቼ በማዘን እና በቁጭት እንኖራለን???
ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ሰሞኑን የጀመረው የውጪ ዜጎችን ኢላማ ያደረገው ጥቃት ተባብሶ መቀጠሉ ተነገረ፡፡ የበርካታ ሀገራት ዜጎች በስለት እታረዱ፣ በእሳት እየተቃጠሉ፣ ንብረታቸው እየተዘረፈና እየወደመ እንዲሁም እየተገደሉ እንደሚገኝ በርካታ የአለም ሚዲያዎች ዜናውን በመቀባበል ላይ ይገኛሉ
ኬንያ ውስጥ ኢትዮጵያኖች በጅምላ እየታሰሩ ነው። ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ኢትዮጵያኖች እየተደበደቡ ፤ በድንጋይ እየተፈነከቱ ፤ በዐይን እንኳን ለማየት በሚሰቀጠጥ ሁኔታ ጎማ ታስሮባቸው ቤንዚል ተርከፍክፎባቸው በእሳት እየተቃጠሉ ነው። የመን ውስጥም እንዲሁ ያለምንም ርህራሄ ኢትዮጵያኖች በግፍ እየተጨፈጨፉ ነው። አምና በሳውዲዎች ላይ "እነዚ እርኩስ አረቦች" እያልን ፀጉር ስንነጭ ፤ ዛሬም "እነዚህ አውሬ ጥቁሮች" እያልን ብናማርር ነገ የወገኖቻችንን እጣ ፈንታ ከዚህ የከፋ ሊሆን ይችላል እንጂ በ"RIP" እና ሌሎች ላይ የስድብ ናዳ በማውረድ ለውጥ አይመጣም።
.
ለዚህ ሁሉ ስደት ፣ ውርደት ፣ ግድያና ሰቆቃ የዳረገን የህወሃት አገዛዝ መሆኑን መገንዘብ አቅቶናል?! ህንድ ፣ ጅቡቲ ፣ ሱዳን እና ሱማልያ ሳይቀሩ ፥ ከነዚህ ሀገራት የራሳቸውን ዜጎች ሲያስወጡ ፤ የኛን ወገኖች ሊያድን ፍላጉቱም አቅሙም ያለው መንግስት የሚባል አካል አለመኖሩ አያንገበግበንም!?
እስከመቼ በማዘን እና በቁጭት እንኖራለን ?? እውነት በወገኖቻችን ጭፍጨፋ ያዘንን ከሆነ ቢያንስ የተደራጁ ሀይሎችን እንርዳ ፣ እናጠናክር ፤ ውርደት ይበቃል እንበል!!
ኬንያ ውስጥ ኢትዮጵያኖች በጅምላ እየታሰሩ ነው። ደቡብ አፍሪካ ውስጥ ኢትዮጵያኖች እየተደበደቡ ፤ በድንጋይ እየተፈነከቱ ፤ በዐይን እንኳን ለማየት በሚሰቀጠጥ ሁኔታ ጎማ ታስሮባቸው ቤንዚል ተርከፍክፎባቸው በእሳት እየተቃጠሉ ነው። የመን ውስጥም እንዲሁ ያለምንም ርህራሄ ኢትዮጵያኖች በግፍ እየተጨፈጨፉ ነው። አምና በሳውዲዎች ላይ "እነዚ እርኩስ አረቦች" እያልን ፀጉር ስንነጭ ፤ ዛሬም "እነዚህ አውሬ ጥቁሮች" እያልን ብናማርር ነገ የወገኖቻችንን እጣ ፈንታ ከዚህ የከፋ ሊሆን ይችላል እንጂ በ"RIP" እና ሌሎች ላይ የስድብ ናዳ በማውረድ ለውጥ አይመጣም።
.
ለዚህ ሁሉ ስደት ፣ ውርደት ፣ ግድያና ሰቆቃ የዳረገን የህወሃት አገዛዝ መሆኑን መገንዘብ አቅቶናል?! ህንድ ፣ ጅቡቲ ፣ ሱዳን እና ሱማልያ ሳይቀሩ ፥ ከነዚህ ሀገራት የራሳቸውን ዜጎች ሲያስወጡ ፤ የኛን ወገኖች ሊያድን ፍላጉቱም አቅሙም ያለው መንግስት የሚባል አካል አለመኖሩ አያንገበግበንም!?
እስከመቼ በማዘን እና በቁጭት እንኖራለን ?? እውነት በወገኖቻችን ጭፍጨፋ ያዘንን ከሆነ ቢያንስ የተደራጁ ሀይሎችን እንርዳ ፣ እናጠናክር ፤ ውርደት ይበቃል እንበል!!
Monday, 13 April 2015
እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ የርሃብ አድማ መቱ
በማዕከላዊ እስር ቤት ታስረው የሚገኙት ብርሃኑ ተክለያሬድና ፍቅረ ማሪያም አስማማው አብራቸው በታሰረችው እየሩስ ተስፋው ላይ እየተፈፀመ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት በመቃወም የርሃብ አድማ መቱ፡፡ ብርሃኑና ፍቅረማሪያም ከትናንት የትንሳኤ በዓል ጀምረው የእርሃብ አድማ ያደረጉ ሲሆን በትናንትናው ዕለት የገባላቸውን ምግብ እንዳልበሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
እየሩሳለም ተስፋው ከሳምንት በላይ ብቻውን እንድትታሰር ተደርጋ ከፍተኛ ምርመራ እየተደረገባት ሲሆን ከቤተሰቦቿ ጋር እንዳትገናኝ ተደርጋለች፡፡ የማዕከላዊ ምርመራ ጥበቃ ፖሊሶች ቤተሰቦቿ ስለ እየሩስ በሚጠይቁበት ወቅት ‹‹መግባት አይቻለም›› ከማለት ውጭ ምክንያቱን እንደማይናገሩም ከቤተሰቦቿ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፡፡
እነ ብርሃኑ እየሩስ ተስፋው ላይ እየተፈፀመ ያለው ኢ-ሰብአዊ ድርጊት እስካልቆመ ድረስ የርሃብ እድማቸውን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡
ወያኔ ካለው በላይ የሚያሳይና ከሚያውቀው በላይ የሚናገር ግብዝ መንግስት መሆኑ....
ዜና /01 07 2007 ዓ.ም
አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ በወያኔ መንግስት ላይ ማንኛውንም ኃይል ወይንም የአፀፋ ግብረ ኃይል በየትኛውም፣ ጊዜ በማናቸውም ቦታ ለማሳረፍ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ፡፡
ሰሞኑን ወያኔ እየፈፀመው ከሚገኘው ከፕሮፖጋንዳ ፍጆታነት የማያልፍ የአየር ላይ ተዋጊ አውሮፕላን ትርኢት፣ የእግረኛና የሜካናይዝድ ውጊያ ልምምድና ከቦታ ቦታ የሠራዊት ጉዞ አንፃ የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ወታደራዊ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር አሰፋ ማሩ
“ወያኔ ካለው በላይ የሚያሳይና ከሚያውቀው በላይ የሚናገር ግብዝ መንግስት መሆኑ ምንጊዜም ቢሆን መዘንጋት የለበትም፡፡” ብለዋል፡፡
ኮማንደር አሰፋ አያይዘውም
“ወያኔ ሁለቱም እግሮቹ ከጉልበቱ ላይ እሱ የህዝቡን አንገት ለመቅላት ከዘር ሰገባ በመዘዘው ስለታም ሰይፍ ተቆርጠው ቁመቱ እጅግ በጣም ድንክ ሆኗል፡፡ ሰው ሰራሽ እግሮች ቀጥሎ ወደ ላይ በመንጠራራት ነው ያደገ ለመምሰል እየሞከረ የሚገኘው፡፡
በህዝቡ ፊት የሚያደርጋቸው ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች የምናብ ፈጠራ ፍሬዎች እንጂ የጦር ሜዳ ዓለም ነፀብራቆች አይደሉም፡፡ አንድ ገበሬ ገና ለገና ንብ ይገባልኛል ብሎ ተስፋ በማድረግ ብቻ በእበት ለቅልቆ በሰም ጭስ በማጠን ትልቅ ዛፍ ላይ በሰቀለው ባዶ ቀፎ የሚመሰለው ህወሓት ያሁን ጊዜ እንቅስቃሴዎቹ ሁሉ በራስ ካለመተማመንና ከፍርሃት የመነጩ ናቸው፡፡ ዛፍ ላይ የተሰቀለ ባዶ ቀፎ ንብ ሳይኖረው ማር በውስጡ ሊከማችበት አይችልም፡፡ መምሰልና መሆን ልዩነታቸው የትየለሌ ነው፡፡ ደግሞም እዩኝ እዩኝ ያለ ቆይቶ ደብቁኝ ደብቁኝ ማለቱ ሳይታልም የተፈታ ነው፡፡” በማለት ገልፀዋል፡፡
ኮማንደሩ እንዳሉትም ወያኔ በእንድ መልክ በወታደራዊ አቅሙ የተባ መስሎ ለህዝቡ ለመታየት ይጣጣራል፤ በሌላ መልኩ ደግሞ እንደ ሸንኮራ መጥጦ ከተፋቸው የቀድሞ ሠራዊት አባላት እግር ስር ሳይቀር እየወደቀ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የህወሓት ጀነራሎች በየመንደሩ እየዞሩ የገበሬ ታጣቂዎችን ዘበመሰብሰብ
“ጦርነት ዓይኑን አፍጥጦ መጥቶብናል፤ ሠራዊታችን እየፈረሰ ወደ ኤርትራ በመኮብለልና የታጠቁ ቡድኖችን በመቀላቀል መዋጋት እንደማይፈልግ አቋሙን እየገለፀልን ነው፡፡ እባካችሁን ባይሆን እናንተ እርዱን አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርግላችኋለን፡፡” እያሉ በመማፀን ላይ እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የአርበኞ ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ወታደራዊ አዣዥ ከማንደር አሰፋ ማሩ
“አርበኞች ግንቦት 7 ህዝቡ እንዲያደርግ የሚፈልገውንና የሚጠበቅበትን ማንኛውንም ተግባር ሁሉ በአስፈላጊው ጊዜና ቦታ ለመፈፀም ዝግጁ ነው፡፡” ካሉ በኋላ
“ህዝቡ ደግሞ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የተጫነውን የባርነት ቀንበር አልሸከምም ብሎ እምቢተኛ መሆንና የትጥቅ ትግሉን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከመደገፍ ባለፈ በባለቤትነት ማስኬዱን በተጠናቀረ ሁኔታ መቀጠል አለበት፡፡” ሲሉ የኢትዮጵያን ህዝብ አሳስበዋል፡፡
ሰሞኑን ወያኔ እየፈፀመው ከሚገኘው ከፕሮፖጋንዳ ፍጆታነት የማያልፍ የአየር ላይ ተዋጊ አውሮፕላን ትርኢት፣ የእግረኛና የሜካናይዝድ ውጊያ ልምምድና ከቦታ ቦታ የሠራዊት ጉዞ አንፃ የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ወታደራዊ መምሪያ አዛዥ ኮማንደር አሰፋ ማሩ
“ወያኔ ካለው በላይ የሚያሳይና ከሚያውቀው በላይ የሚናገር ግብዝ መንግስት መሆኑ ምንጊዜም ቢሆን መዘንጋት የለበትም፡፡” ብለዋል፡፡
ኮማንደር አሰፋ አያይዘውም
“ወያኔ ሁለቱም እግሮቹ ከጉልበቱ ላይ እሱ የህዝቡን አንገት ለመቅላት ከዘር ሰገባ በመዘዘው ስለታም ሰይፍ ተቆርጠው ቁመቱ እጅግ በጣም ድንክ ሆኗል፡፡ ሰው ሰራሽ እግሮች ቀጥሎ ወደ ላይ በመንጠራራት ነው ያደገ ለመምሰል እየሞከረ የሚገኘው፡፡
በህዝቡ ፊት የሚያደርጋቸው ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች የምናብ ፈጠራ ፍሬዎች እንጂ የጦር ሜዳ ዓለም ነፀብራቆች አይደሉም፡፡ አንድ ገበሬ ገና ለገና ንብ ይገባልኛል ብሎ ተስፋ በማድረግ ብቻ በእበት ለቅልቆ በሰም ጭስ በማጠን ትልቅ ዛፍ ላይ በሰቀለው ባዶ ቀፎ የሚመሰለው ህወሓት ያሁን ጊዜ እንቅስቃሴዎቹ ሁሉ በራስ ካለመተማመንና ከፍርሃት የመነጩ ናቸው፡፡ ዛፍ ላይ የተሰቀለ ባዶ ቀፎ ንብ ሳይኖረው ማር በውስጡ ሊከማችበት አይችልም፡፡ መምሰልና መሆን ልዩነታቸው የትየለሌ ነው፡፡ ደግሞም እዩኝ እዩኝ ያለ ቆይቶ ደብቁኝ ደብቁኝ ማለቱ ሳይታልም የተፈታ ነው፡፡” በማለት ገልፀዋል፡፡
ኮማንደሩ እንዳሉትም ወያኔ በእንድ መልክ በወታደራዊ አቅሙ የተባ መስሎ ለህዝቡ ለመታየት ይጣጣራል፤ በሌላ መልኩ ደግሞ እንደ ሸንኮራ መጥጦ ከተፋቸው የቀድሞ ሠራዊት አባላት እግር ስር ሳይቀር እየወደቀ ይገኛል፡፡ በተጨማሪም የህወሓት ጀነራሎች በየመንደሩ እየዞሩ የገበሬ ታጣቂዎችን ዘበመሰብሰብ
“ጦርነት ዓይኑን አፍጥጦ መጥቶብናል፤ ሠራዊታችን እየፈረሰ ወደ ኤርትራ በመኮብለልና የታጠቁ ቡድኖችን በመቀላቀል መዋጋት እንደማይፈልግ አቋሙን እየገለፀልን ነው፡፡ እባካችሁን ባይሆን እናንተ እርዱን አስፈላጊውን ድጋፍ እናደርግላችኋለን፡፡” እያሉ በመማፀን ላይ እንዳሉ ለማወቅ ተችሏል፡፡
የአርበኞ ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ ወታደራዊ አዣዥ ከማንደር አሰፋ ማሩ
“አርበኞች ግንቦት 7 ህዝቡ እንዲያደርግ የሚፈልገውንና የሚጠበቅበትን ማንኛውንም ተግባር ሁሉ በአስፈላጊው ጊዜና ቦታ ለመፈፀም ዝግጁ ነው፡፡” ካሉ በኋላ
“ህዝቡ ደግሞ ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ የተጫነውን የባርነት ቀንበር አልሸከምም ብሎ እምቢተኛ መሆንና የትጥቅ ትግሉን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ ከመደገፍ ባለፈ በባለቤትነት ማስኬዱን በተጠናቀረ ሁኔታ መቀጠል አለበት፡፡” ሲሉ የኢትዮጵያን ህዝብ አሳስበዋል፡፡
በማህበራዊ ድረ-ገፆች አማካኝነት ነፃነት በተራቡ ወጣቶች ቀስቃሽ ነት የተጀመረው ዝርዝር ሳንቲሞችን በመሰብሰብ ለወያኔ መንግስት ፍፁም አምባገነናዊ አገዛዝ እምቢተኛነትን የመግለፅ ሂደቱ አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡
በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ከተሞች የሚኖሩ እምቢተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች በትንሹ የ3 መቶና የ4መቶ ብር ሳንቲሞች በየጓዳው እያከማቹ ተቃውሟቸውን በመግለፅ ላይ ይገኛሉ፡፡ አንድ ብር በ0.75 ሳንቲም መመንዘር የጀመረባቸው ከተሞች እንዳሉም ታውቋል፡፡
በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ከተሞች የሚኖሩ እምቢተኛ የህብረተሰብ ክፍሎች በትንሹ የ3 መቶና የ4መቶ ብር ሳንቲሞች በየጓዳው እያከማቹ ተቃውሟቸውን በመግለፅ ላይ ይገኛሉ፡፡ አንድ ብር በ0.75 ሳንቲም መመንዘር የጀመረባቸው ከተሞች እንዳሉም ታውቋል፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)