Saturday, 31 December 2016

በውጭ ብድር የተጀመሩ የስኳር ፋብሪካዎች ግንባታቸው ሳይጠናቀቅ የብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ


ኢትዮጵያን ስኳር ላኪ ሃገር ያደርጋሉ ተብለው ከውጭ በተገኘ ከ70 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር ግንባታቸው ከሰባት አመት በፊት የተጀመሩ ፋብሪካዎች ግንባታቸው ተስተጓጉሎ እያለ ብድር የመክፈያ ጊዜያቸው መድረሱ ተገለጸ።

በከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እጥረት ውስጥ የሚገኘው መንግስት በበኩሉ በመገንባት ላይ ያሉትን ጨምሮ በስራ ላይ ያሉ የስኳር ፋብሪካዎች ከውጭ ባለሃብቶች ጋር በሽርክና ለመስራው መወሰኑን ይፋ አድርጓል።

መንግስት ከተለያዩ አበዳሪ የፋይናንስ ተቋማት በብድር ባገኘው ገንዘብ የወልቃይት፣ የኦሞ፣ ኩራዝ አንድ ሁለትና ሶስት እንዲሁም የጣና በለስ ቁጥር አንድና ሁለት ፕሮጄክቶችን ለመገንባት እንቅስቃሴ መጀመሩ ይታወሳል።

ይሁንና ሃገሪቱን ከስኳር እጥረት በማላቀቅ ኢትዮጵያ ምርቷን ወደ ውጭ ሃገር በመላክ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሪ እንድታገኝ ያደርጋሉ ተብሎ ተስፋ የተጣለባቸው ፋብሪካዎች አብዛኞቹ በጅምር ላይ መቅረታቸው ተመልክቷል።

ፋብሪካዎቹ በከፍተኛ የፋይናንስ እጥረት ውስጥ በመግባታቸውና የተጀመሩ ፕሮጄክቶችን ለማስጨርስ ተጨማሪ የውጭ ምንዛሪ በማስፈለጉ ምክንያት መንግስት ነባሮቹንና አዳዲስ ግንባታዎች በሽርክና ለማካሄድ መወሰኑን የመንግስት መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ፋብሪካዎቹ በአምስት አመት ውስጥ ወደ ምርት ይገባሉ ተብሎ የተጠበቁ ሲሆን፣ ግንባታቸው በ25 በመቶ ላይ የሚገኝ እንዳለም የኢትዮጵያ ስኳር ኮርፖሬሽን መረጃ ያመለክታል።

ፋብሪካዎች ለሰባት አመት ያህል መጠናቀቅ ባለመቻላቸው ከአበዳሪ ካላት የተገኘ ብድር የመጀመሪያ ክፍያ የመጀመሪያ ጊዜው መቃረቡን ኮርፖሬሽኑ አስታውቋል።

የኮንትራት አስተዳደርና የፋይናንስ ችግሮች ፋብሪካዎቹ በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ እንዳይጠናቀቁ ካደረጉ ምክንያቶች መካከል ዋነኞቹ መሆናቸውን የኮርፖሬሽኑ የኮሙኒኬሽን ሃላፊ የሆኑት አቶ ጋሻው አይችሉህም ለሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ገልጸዋል።

በሃሙስ ዘገባችን ለጣና በለስ የስኳር ፋብሪካ ተዘጋጅቶ የነበረ የሸንኮራ አገዳ ምርት ፋብሪካው ባለመጠናቀቁ ምክንያት ምርቱ እንዲቃጠል መደረጉን መዘገባችን ይታወሳል።

ከፋብሪካው በፊት ለምርት ደርሶ የነበረው የሸንኮራ አገዳ እንዲወገድ የተወሰነው ምርት ከፍተኛ ገንዘብ የፈሰሰበት እንደነበር ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው አካላት ይገልጻሉ።

በሃገሪቱ ያሉ ጅምርና ነባር የስኳር ፋብሪካዎችን ከውጭ ባለሃብቶች ጋር በሽርክና ለማስተዳደር የቻይንና የአውሮፓ ሃገራት በመደራደር ላይ ሲሆን፣ መንግስት ያጋጠመው የፋይናንስ እጥረት ወደዚህ አማራጭ እንዲገባ ማስገደዱንም ባለሙያዎች አስተድተዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም የጣና በለስ አንድና ሁለት የስኳር ፕሮጄክቶችን ለአንድ የቱርክ ኩባንያ 75 በመቶ ድርሻን ለመስጠት ሲካሄድ የነበረ ድርድር መቋረጡም ታውቋል።

በዲሳ ግሩፕ የተሰኘ ይኸው የቱርክ ኩባንያ ወደ አንድ ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ገንዘብ በመመደብ የፕሮጄክቱን 75 በመቶ ባለቤትነት ለመረከብ ድርድር ጀምሮ የነበረ ሲሆን፣ ከገንዘብ አከፋፈልና ከትርፉ ክፍፍል ጋር ከመንግስት ጋር ሊደርስ አለመቻሉ ተገልጿል።

ይሁንና ሁለቱም ወገኖች ተፈጥሯል በተባለው አለመግባባት ዙሪያ ዝርዝር መረጃን ከመስጠት ተቆጥበዋል።

ኢሳት

Tuesday, 22 November 2016

አንድ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በትግራይ ተወላጅ ተማሪ ዘግናኝ ጥቃት ተፈፀመበት

አንድ የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ተማሪ በትግራይ ተወላጅ ተማሪ ዘግናኝ ጥቃት ተፈፀመበት።
በተመሳሳይ ህዳር 21 ያልተጠበቀ ጥቃት ሊፈፅሙ መዘጋጀታቸውን በቅርብ የሚከታተሏቸው ተማሪዎች መረጃውን አውጥተውታል።
የትግራይ ተውላጅ ተማሪዎች ሌሎች ተማሪዎችን መተንኮል ጀምረዋል።በተለይ በዚህ ሁለት ቀን ውስጥ ተደጋጋሚ ትንኮሳዎችን አድርገዋል። ከነዚህም መካከል አክሊሉ መንገሻ የተባለ የ3ኛ አመት ማኔጅመት ተማሪ ትናንት ምሽት ጆሮውን_ቆርጠውታል፤ ልጁም ለህክምና ወደ አዲስ አበባ ተልኳል፤ወንጀል ፈፃሚውም በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውሏል ተብላል።
ቆራጩ ትግሬ ሲሆን አክሊሉ ግን የአቦምሳ (ናዝሬት አካባቢ) ልጅነው ፡፡ ልጁ ለህክምና  ወደ አዲስ አበባትናንት የተላከ ሲሆን የኢትዮ ስታር ሆቴል ባለቤት(ትግሬ )  ለማደራደር በሽምግልና ቢመጡም አልተሳካም።ሌላ ደግሞ የአደት ልጅ 3ኛ አመት ማርኬትንግ ተማሪም እንድሁ ጥቃት ሊያደርሱበት ሞክረው ሳይሳካላቸው ቀርቷል ፡፡ በተለይ ትናንትና ዛሬ ብዙ ተማሪዎችን ሲተናኮሉና ሲደባደቡ ነበር።
በዚህ አጋጣሚ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች እርስበርሳችሁም ሆነ ሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጋር አፋጣኝ መረጃ ትለዋወጡ ዘንድ እንመክራለን።

Sunday, 16 October 2016

ሰበር_መረጃ አስቸኳይ የፋይናንስ አዋጅ ሊታወጅ እንደሆነ ተሰማ

ሰበር_መረጃ….አስቸኳይ የፋይናንስ አዋጅ ሊታወጅ እንደሆነ ተሰማየብሔራዊ ባንክ ውጭ ምንዛሪ ካዝና ባዶ ነው

October 16, 2016

የኢህአዴግ ጽ/ቤት በትርምስና የእርስ በእርስ ውንጀላ ላይ ነው። በውጪ እና በሀገር ውስጥ ኢንቬስተሮች ከኤክስፖርት ይገኝ የነበረው የውጭ ምንዛሪ በ5 ወራት ውስጥ በ71.1 በመቶ በመቀነሱ ለመጀመሪያ ጊዜ የ1.9 ቢሊዮን ዶላር የገቢ ውድቀት ታይቷል። ከተጠበቀው በታች በመቀነሱ ይሄንን የህዝብ አገልግሎት ሰጪ የሆኑ የትምህርት ቤት በጀት (የመምህራን ደሞዝን ጨምሮ)፣ የጤና አገልግሎት፣ ትራንስፖርት፣ ከፍተና ወጪ ያስከተለው የፖሊስ ሰራዊትና የወታደሮች ደሞዝ በዚህ የበጀት ቀውስ ምክንያት በመስተጓጎሉ አዲስ አዋጅ ማስፈለጉ ተሰምቷል።

ከሁሉም አስከፊ የሆነው ከቻይና ሌሎች አበዳሪዎች ለኢንቨስትመንስት ጉዳይ ተብሎ የተገኘው ብድር 16 ቢሊዮን ዶላር በመድረሱ በመጀመሪያው የክፍያ በ2016 አመት አስከፊ የፋይናንስ ቀውስ መገባቱ ምክንያት ሆኗል። ኢትዮጵያ በአሳሳቢ የዕዳ ሽክም ከአለም 11ኛ ሆናለች። ከዚህ ባለፈ ለውድቀቱ ተጨማሪ ምክንያት የሆነው እርዳታ ሰጪ ሀገሮች በየጊዜው የሚያስገኙት የበጀት ድጋፍ እየቀነሰ በመምጣትና ወደ ሰብዓዊ አስቸኳይ የምግብ ርዳታ ላይ ትኩረት በማድረጋቸው መሆኑም ጭምር ነው።
http://www.satenaw.com/amharic/archives/23331

Monday, 3 October 2016

የኢሬቻ በዓል ጭፍጨፋ

ፕሮፌሰር መስፉን ወ/ማሪያም
የኢሬቻ በዓል ጭፍጨፋ፡--- እንደሰው ያሳዝነኛል፤ ያሳፍረኛል፤ እንደኢትዮጵያዊ ዜጋ ያዋርደኛል፤ ያሳጣኛል፤ አለኝ የምለውን የጨዋነት ባህል፣ ይሉኝታና ክርስስቲያናዊ ሰብአዊነት ያጎድፍብኛል፤ ራቁቴን በዓለም ሕዝብ ፊት ያቆመኝ ይመስለኛል፡፡
ለሥልጣን ብዙ ሰዎች ሰዎችን አጫርሰዋል፤ ብዙ ንብረትን አውድመዋል፤ የብዙ ሕዝቦችን የእድገት እርምጃ አግደዋል፤ ወደኋላም መልሰዋል፤ ሞት እየቀጠፋቸው ሥልጣናቸው ባልወደዱት እጅ ገብቷል፡፡
ለሀብት ብዙ ሰዎች ሰዎችን አጫርሰዋል፤ ከሰው ልጅ ሕይወት፣ ከሰው ልጅ ምቾት ሀብት በልጦባቸው ጤንነታቸውን እያጡ በማያሸንፉት ሞት ተቀጥፈዋል፤ ከሰው ልጅ የበለጠባቸው ሀብት እንኳን ለነሱ ለልጆቻቸውም ሳይሆን ተዝረክርኮ ቀርቷል፡፡
የባለሥልጣንና የሀብታሞች ሎሌ በመሆን ወንድም ወንድሙንና እኅቱን ገድሎ፣ ጎረቤቶቹንና ወገኖቹን አስቀይሞ ከውርደት ኑሮ በቀር ክብርንና ኩራትን አያገኝም፤ የሠራውን ሥራ፣ ወንድሙን ወይም እኅቱን መግደሉን፣ ከእሱ በቀር የሚያውቀው የለም ይሆናል፤ ይህ አእምሮውም ውስጥ ልቡም ውስጥ የተለጠፈ እውቀት በመቃብርም ሆነ ከመቀብር ውጭ አይለየውም፤ ማናቸውንም ምቾት ይነሳዋል፡፡
መግደልም ሆነ ማስገደል የመጨረሻው የውድቀትና የጻዕር ምልክት ነው፤ ወይም የታቀደ የመጨረሻው እልቂት መጀመሪያ ነው፤ የተጠቂው ወገን ሲመርረው አጥቂው ካልጎመዘዘው፣ አጥቂው እስቲጎመዝዘው ድረስ የተጠቂው ምሬት ቋቅ እስቲለው ይቀጥላል፤ የተጠቂው ምሬት ቋቅ የሚያስደርግ ደረጃ ላይ ሲደርስ የአጥቂውም መጎምዘዝ ወደምሬት ያሸጋገራል፤ ትእግስት የጎደለው የአጥቂ ጉልበተኛ ምሬትና ቋቅ የሚል የተጠቂ ምሬት ሲጋጠሙ ውጤቱ እልቂት ነው፤ ጉልበተኛ ጉልበቱ እስቲሰበር የሞተ ኅሊና (እንጉርጉሮ ወይም አሁንም እንጉርጉሮ) በሚለው ግጥሜ በከፊል የሚከተለውን ብዬ ነበር፡---
ከሳሽ፣ ተከሳሽ፣ ዳኛ መሆን
እንዴት ይችላል መበየን?
ሲፍነው ግን ኅሊናውን፣
አይለይም ጨለማውን ከብርሃን!
ኅሊናውን የገደለ ሰው
ማን ሊቀረው? ምን ሊያቅተው?
የጉልበቱ መሣሪያ ነው፤
ጊዜ ጉልበቱን እስቲሰብረው!
እግዚአብሔር ከመጨካከን ፉክክር ይጠብቀን፡፡

Friday, 2 September 2016

#ኮንሶ #አርባምንጭ

Breaking News
    #ኮንሶ
    #አርባምንጭ
 ህዝባዊው ንቅናቄ ወደ ደቡብም እየገባ ነው። በኮንሶ እና አርባምንጭ ለሦስት ቀን ከቤት ያለመውጣት ተቃውሞ
ተጠርታል በዚህ ተቃውሞ መላው የኮንሶ የአርባምንጭ ህዝብ ከወገኑ የአማራና የኦሮሞ ህዝብ ጎን መቆሙን የሚያሳይበት ነው ተብሏል። የከተማው ወጣቶች የወያኔን ገዳይ ስርአት በመቃወም የሚታወቁ ሲሆን በዚህም ቂመኛው የወንበዴ ቡድን በከተማው ነዋሪ ላይ ከፍተኛ ግፍ መፈፅማቸው ይታወቃል አርባምንጭ ይለያል ዘንድሮ የወያኔ ኑሮ ያሉ ነው።

Wednesday, 31 August 2016

Ethiopian regime deploying massive military to the Amhara region as uprising continue unabated

Ethiopian regime deploying massive military to the Amhara region as uprising continue unabated
By Engidu Woldie
ESAT News (August 31, 2016)
Reports reaching ESAT from Ethiopia say the TPLF regime is deploying thousands of its troops and Agazi Special Forces to the Amhara region where uprising against the regime is gaining momentum as more towns and localities removed local administrations and the security, and replaced them with interim administrations elected by the people.
Thousands of troops in a dozens of convoys and heavy machinery were seen heading towards northern Gondar via Wuchale, Wollo as the alternative and direct routes were closed by protesters, according to a sources who spoke to ESAT.
ESAT is yet to verify the information but high ranking TPLF military and civilian officials led by chief of staff Samora Yunis have arrived in Gondar. Close observers of the new developments say the regime was heading towards forming military posts and putting in place a military administration as seen in the Oromo region of the country where a nine month protest has relatively quieted this month.
Deadly protests have however continued on Tuesday in Gondar and Gojam where seven protesters - three in Adet and four in Simada - were shot and killed by TPLF forces. Three people were also killed in Merawi.
In Bahir Dar, angry protesters went to the Sebatamit prison and freed 700 prisoners who were detained in the recent protests. Several people were injured in the shoot out to free the prisoners, according to hospital sources. Gun fire could be heard on Tuesday in the city of Bahir Dar which saw deadly protests on Monday as four people were killed and protesters attacked businesses belonging to the regime.
In Amba Giorgis, regime forces attacked residents who on Monday targeted businesses and set on fire houses belonging regime officials.
Tensions remained high in Fnote Selam that has seen deadly protests in recent days. Offices and businesses remained closed on Tuesday in Finote Selam.
Prime Minister Hailemariam Desalegn blamed the unrest on what he called “foreign forces” bent on distracting the country from its development and fomenting ethnic conflicts. He declined to name the “foreign forces” but went on to accuse them of providing financial support to Ethiopian opposition forces in the diaspora.
The Premier’s accusations did not come as a surprise to political observers who said that it has been customary for the regime to blame external forces for all its internal crises.
Meanwhile, human rights groups called for an independent investigations into the killings and incarceration of civilians by security forces in Ethiopia. Defend Defenders, Amnesty International, Ethiopian Human Rights Project, Frontline Defenders and FIDH called in a joint statement for the immediate cessation of the killings and detention of peaceful citizens and members of the civic society.

Friday, 22 July 2016

ህወሓት አማራ ቴሌቪዥንን ዘጋ

ሰበር ዜና
ህወሓት አማራ ቴሌቪዥንን ዘጋ፡፡
ህወሓት በአማራ ክልል መንግስት ከመናደዱ የተነሳ እሱ በሚቅጣጠረው ቴሌ አማካኝነት የቴሌቪዥን ጣቢያው ከናይል ሳት እንዲቋረጥ አድርጓል፡፡ እንደ አማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ገለፃ ከሆነ ምክኒያቱ ከዚህ በታች የተጠቀሰው ነው፡-
የአማራ ቴሌቪዥን በናይል ሳት ሳተላይት ስርጭቱን ለተመልካቹ እንደሚያደርስ ይታወቃል፡፡ የሳተላይት ክፍያው ለመፈፀም ደግሞ የአማራ ብዙሃ መገናኛ ድርጅት ለኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በወቅቱ ይከፍላል፡፡ ኢብኮ ደግሞ ለኢትዮ ቴሌኮም ክፍያውን ያስገባል፡፡ በዚህ ሂደት ላለፉት 2 አመታት የተፈፀመውን ክፍያ ኢትዮ ቴሌኮም ለሳተላይት አከራዩ ድርጅት ባለመክፈሉ የአማራ ቴሌቪዥን ስርጭቱ ዛሬ ንጋት ጀምሮ ተቋርጧል፡፡ ይላል፡፡ ሆኖም አሁን ላይ መሆኑ የጎንደሩን ጉዳይ አሸባሪ ምናምን እያለ እንደ ህወሓት ባለማስጮሁ ተበሳጭተው እድርገውት ይሆናል፡፡ ህወሓት የአማራ ክልል መንግስትን ውስጡ ገብታ መፈረካከስ ቢያቅጣት ብቸኛውን የአማራ ቴቬ ዘጋችው!
የፌደራል መንግስቱን መጠቀሚያ በማድረግ አማራ ክልልን ማጥቃት ቀጥላለች፡፡ የሚገርመው ከመንግሥት ሚዲያዎች አማራ ቴቪ ነበር የምመለከተው፡፡ ለጊዜው ሌላ አማራጭ አያለሁ፡፡ ፈቅደው ከከፈቱላቸው ሃሃሃሃ ገና ብአዴንና ህወሓት ወደ ጦርነት ሳይገቡ አይቀርም በዚህ አያያዝ፡፡ ምክኒያቱም የህወሓት ጥጋብና ትዕቢት ወሰን አጥቷልና፡፡ ነገ ደግሞ ምን ሊዘጉ ይሆን?
የድጎማ በጀት?