Monday 18 September 2017

The Intercept የሚባለው ሚስጥር አውጪ ህውሃት በበላይነት የሚመራው የኢትዮጵያ መንግስትን ሚስጥር ማስፈትለኩን ታወቀ

የአሜሪካንና የሌሎች መንግስታትን ድብቅና ከፍተኛ ሚስጥር በማጋለጥ የሚታወቀው ዘ ኢንተርሴፕት (The Intercept)የሚባለው ሚስጥር አውጪ (Whistle blower) በመስከረም 13 ቀን 2017 እኤአ ህውሃት በበላይነት የሚመራው የኢትዮጵያ መንግስትን ሚስጥር ማስፈትለኩን ታወቀ።

ይህን በሃይለማርያም ደሳለኝ ቁንጮነት የሚመራው የኢትዮጵያ መንግስት ጥብቅ ሚስጥርን ይዞ ወደ አደባባይ የወጣው በአሜሪካ መንግስት ተፈላጊ ከሆኑ ግለሰቦች መካከል በቀዳሚነት የተሰለፈው የቀድሞው የስለላ አባል የሆነው ኤድዋርድ ስኖውደን (Edward Snowden)እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።
ኤድዋርድ ስኖውደን በአሜሪካ መንግስት በከፍተኛ ሚስጥርነት የተያዙትን መረጃዎች ለዊክሊክስ በማስተላለፉ ምክንያት በሩሲያ የጥገኝነት ህይወት እየመራ እንደሚገኝ ይታወቃል።
የአሜሪካ መንግስት በስልጣን ላይ ካለው የህውሃት አገዛዝ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ ምድር እያደረገ ያለውን ከፍተኛ የስለላ ሚስጥር መረጃ ዘ ኢንተርሴፕት (The Intercept) በተባለው የሚስጥር አውጪ ሊጋለጥ መቻሉን ለመረዳት ተችሏል።
ዘ ኢንተርሴፕት (The Intercept) ይህን ጥብቅ መረጃ ያገኘው ከኤድዋርድ ስኖውደን የሚስጥር ፋይል እንደሆነም ገልጿል።
በመንግስታቶች የሚከናወኑ ከፍተኛ ሚስጥሮችን (classified information) በማጋለጥ የሚታወቀው ዘ ኢንተርሴፕት(The Intercept) በመስከረም 13 ቀን 2017እኤአ ለህትመት ባወጣው ዶክመንት የአሜሪካው የስለላ አካል የሆነው NSA (National Security Agency) ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር በመተባበር በምስራቅ አፍሪቃ ግዙፍ የስለላ ተቋም መገንባቱ በማስረጃ ለአለም አሳውቋል።
ይህ ዘመናዊ መሆኑ የተነገረለት የስለላ ተቋም ኢትዮጵያኖችን ጨምሮ በምስራቅ አፍሪቃ የሚገኙ አጎራባች አገራት የሚያደርጉትን እንቅስቃሴዎች እንዲሁም የሚያደርጉትን የስልክና የኢንተርኔት ንግግሮች ወይም ግንኙነቶች በመጥለፍ የስለላ ተግባሩን እንደሚያከናውን ዘ ኢንተርሴፕት(The Intercept) አጋልጧል።
NSA (National Security Agency) በመባል የሚታወቀው የአሜሪካ የስለላ ተቋም የኢትዮጵያ መንግስት ላበረከተለት የቦታ እና የሰው ሃይል ስጦታ ውለታን በውለታ ለመመለስ የአምባገነኑን የኢትዮጵያ ሃይሎችን በኤሌትሮኒክ ሰለላ (electronic surveillance) ስለጠና መስጠቱ በዶክመንቱ ተጋልጧል::
የኢትዮጵያ መንግስት የኤሌክትሮንክስ የስለላን ዘዴ የተጠቀመበት ሽብርተኝነትን ወይንም ደግሞ ወንጀልን ለመዋጋት ሳይሆን የገዛ ዜጋውን ወይም ህዝቡን ለማሰቃየት እንደሆነ ዘ ኢንተርሴፕት (The Intercept) ከፍተኛ የሆኑ የሰብአዊ መብት ተመራማሪ የሆኑትን Mr. Felix ጠቅሶ ዘግቧል።
የአሜሪካው National Security Agency በየካቲት 2002እኤአ በአዲስ አበባ ከተማ የመጀመሪያውን የአንበሳ ኩራት (Lion’s Pride) ተብሎ የሚጠራውን የስለላ ማዕከል ማቋቋሙን ይህ ዶክመንት ይጠቁማል።
ይህ የስለላ ማዕከል እንደተቋቋመ ቀለል ያለ ሚሽን (ተልእኮ) የሚመሩ አስራ ሁለት ኢትዮጵያውያኖች ብቻ እንደነበሩትም ተዘግቧል።
ነገር ግን በ2005እኤአ ይህ ቁጥር በሚያስገርም ሁኔታ አድጎ ስምንት የአሜሪካ ወታደራዊ ፕርሶኔል እና መቶ ሶስት ኢትዮጵያዊያኖች ተሰማርተው እንደሚገኙ ለመረዳት ተችሏል።
ከዚህም በተጨማሪ ማዕከሉ ወደ አርባ ስድስት የሚሆኑ የስራ ቦታዎች እንደነበሩት ይሄው ዶክመንት አያይዞ ገልጧል።
ዘ ኢንተርሴፕት ያወጣው ሚስጥራዊው ዶክመንት እንደሚጠቁመው የአሜሪካው የስለላ አካል የሆነው NSA አዲስ አበባ ከሚገኘው የስለላ ማእከሉ በተጨማሪ በድሬዳዋም በ2006እኤአ ሁለተኛውን የሰለላ ተቋም መዘረጋቱን ለማወቅ ተችሏል።
በድሬዳዋ የተቋቋመው የስለላ ማዕከል በህዝቦች መካከል የሚደረገውን ግንኙነት በተለይ ደግሞ በሶማልያ፣ ሱዳን እና በምስራቅ ኢትዮጵያ የሚደረጉ ማንኛውንም የኤሌክትሮኒክ ግንኙነትን ወይም ንግግርን የሚያዳምጥ መሆኑን ይሄው ዶክመንት አስፍሯል።
በሌላ በኩል ደግሞ የአሜሪካ መንግስት እና የኢትዮጵያ መንግስት በመተባብር በኡጋዴንና በሶማሊያ ጠረፍ እካባቢ የሚደረገውን የህዝቦች ግንኙነት የድሬዳዋውን ማዕከል በመጠቀም መሰለላቸውን ሚስጥራዊው ማስረጃ ያትታል።
የጥቁር ኩራት ወይም Lion’s pride ተብሎ የሚጠራው የስለላ ማዕከል በአዲስ አበባ እና በድሬዳዋ ከተመሰረቱት ማዕከላት በተጨማሪ በጎንደር አካባቢም ሶስተኛ ማዕከል መከፈቱን የኢንተርሴፕት Intercept የምርምር ዶክሜንት ጨምሮ ገልጧል።
የአሜሪካ የስለላ ድርጅት በዑጋዴን አካባቢ የሚደረገውን እንቅስቃሴ በመሰለል የኢትዮጵያ መንግስት በንጹሃን ዜጎች ላይ ለፈጸመው አሰቃቂ ግድያ ተባባሪ መሆኑ እጅግ በጣም አስነዋሪ ነው በማለት የሰብአዊ መብት ተመራማሪ የሆኑት Mr. Horne ቅሬታቸውን ገልጸዋል።
ዘ ኢንተርሴፕት the Intercept ባወጣው በዚህ ዶክመንት በአሁኑ ሰአት እነዚህ ከአሁን በፊት በአዲስ አበባ ፣ በድሬዳዋ እንዲሁም በጎንደር የተከፈቱት የስለላ ማእከላት መዘጋታቸውን የሚያሳይ ምንም ማስረጃ እንዳላገኘ ዘግቧል።
አያይዞም የአሜሪካ መንግስት ከዚህ አሳፋሪ እና ህገወጥ ድርጊቱ መቆጠብ ይኖርበታል ሲል አሳስቧል።

No comments:

Post a Comment